የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በካፋ ዞን የሻይ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በይፋ ተጀመረ

Aug 4, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ካፋ፤ሐምሌ 27/2018 (ኢዜአ)፦ በካፋ ዞን የሻይ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በዛሬው ዕለት በይፋ ተጀመረ።

የሻይ ችግኝ ተከላ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር በካፋ ዞን ሺሾ እንዴ ወረዳ ዋና ቦላ ቀበሌ በዛሬው እለት ተከናውኗል።

በዚሁ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ፤ የሻይ ልማትን ለማስፋት የተያዘውን እቅድ መሰረት በማድረግ በዞኑ አራት ወረዳዎች ችግኝ የማዘጋጀት ስራ ሲሰራ መቆየቱን ገልጸዋል።


በመሆኑም በአራት የችግኝ ጣቢያዎች 1 ነጥብ 8 ሚሊዮን የሻይ ችግኞች መዘጋጀታቸውን አንስተው የመትከል ስራው በዛሬው እለት በይፋ መጀመሩን ተናግረዋል።

በዚሁ መሰረትም ከዛሬ ጀምሮ በቀጣዮቹ ተከታታይ 15 ቀናት በተዘጋጀው 110 ሄክታር መሬት ላይ የመትከል ስራው የሚከናወን መሆኑን ገልጸዋል።

የሺሾ-እንዴ ወረዳ ግብርና አካባቢ ጥበቃና ሕብረት ስራ ልማት ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ አዱኛ አለሙ፤ በበኩላቸው በወረዳው የአየር ንብረት ለውጥን ከመቋቋም በተጨማሪ ለምግብነት የሚውሉ የፍራፍሬና የውጭ ምንዛሬን ለማያስገኙ ለቡናና ሻይ ችግኞች ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል።


ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ ከአረንጓዴ አሻራ ኢንሼቲቭ ጋር በማያያዝ የሻይ ችግኞችን በማዘጋጀት በዛሬው እለት በዋና ቦላ ቀበሌ ተከላ መጀመሩን ገልጸዋል።

በወረዳው 43 ነጥብ 5 ሄክታር መሬት ለሻይ ልማት መዘጋጀቱን ጠቅሰው የችግኝ ተከላው ይቀጥላል ብለዋል።

በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ለይ የተገኙት የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ቡና፣ ሻይና ቅመማ ቅመም ባለሥልጣን ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ካሳሁን ታዬ፤ በክልሉ በዘንድሮው ዓመት ለሻይ ልማት ልዩ ትኩረት በመስጠት የተሟላ ዝግጅት በማድረግ ወደ ስራ መገባቱን ተናግረዋል።

በተያዘው እቅድ መሰረትም ዘንድሮ የሻይ ችግኝ ተከላ በብዛት የሚከናወን ይሆናል ብለዋል።


ከዋና ቦላ ቀበሌ ነዋሪዎች መካከል አርሶ አደር ጌታቸው ወልደጊዮርጊስ እና አቶ ንጉሴ ገብረሚካኤል የልማት ስራው በብዙ መልኩ ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026