🔇Unmute
አዲስ አበባ፣ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ)፡-በክልሉ በተያዘው የበጀት ዓመት የገበያ የክትትልና ቁጥጥር ስራዎች በማጠናከር እንዲሁም የግብርናና ኢንዱስትሪ ምርቶች አቅርቦት እንዲሻሻል በማድረግ የኑሮ ጫናን ለማቃለል በትኩረት እንደሚሰራ የሐረሪ ክልል ንግድ ልማት ኤጀንሲ አስታወቀ።
የሐረሪ ክልል ንግድ ልማት ኤጀንሲ ኃላፊ አቶ ሸሪፍ ሙሜ በበጀት አመቱ በሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት ላይ መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም በያዝነው የበጀት አመት በክልሉ የኑሮ ጫናን ለማቃለል የሚያስችሉ ስራዎች በተጠናከረ መልኩ ይከናወናሉ ብለዋል።
በተለይም የገበያ የክትትልና ቁጥጥር ስራዎች በማጠናከር የግብርናና ኢንዱስትሪ ምርቶች አቅርቦት እንዲሻሻል የማድረግ ስራዎች የላቀ ትኩረት ይሰጣል ብለዋል።
ሸማቹን ማህበረሰብ ለአላስፈላጊ ወጪና ለእንግልት የሚዳርጉ ሰው ሰራሽ የዋጋ ጭማሪዎች የሚያደርጉ ነገዴዎች ተጠያቂ እንዲሆኑ የማድረግ ስራ ይሰራል ነው ያሉት።
የምርት አቅርቦትን በማሻሻል፣ የገበያ ሰንሰለት ማነቆዎችን በመፍታትና ህገ-ወጥ ንግድን የመቆጣጠር ስራዎችም ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት እንደሚሰራ ጠቁመዋል።
የቅዳሜና እሁድ ገበያን በማጠናከር የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶችና የኢንዱስትሪ ውጤቶችን በቀጥታ ለሸማቹ በማቅረብ የኑሮ ጫናን ለማቃለል እንደሚሰራ ተናግረዋል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026