የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ተጨማሪ ሃብት ለማፍራት አስችሎናል-ተጠቃሚዎች

Aug 17, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጎንደር፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ) ፡-የሌማት ትሩፋት መርሃ-ግብር ኑሯቸውን ለመለወጥና ተጨማሪ ሀብት ለማፍራት እንዳስቻላቸው በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ተጠቃሚዎች ገለጹ።

የሌማት ትሩፋት የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ፣ የሥነ-ምግብ ደረጃን ለማሻሻልና አጠቃላይ የግብርና ምርታማነትን በጥራትና በብዛት ለማሳደግ ያለመ ሀገራዊ ንቅናቄ ነው።

መርሃ-ግብሩ በተለይም በወተት፣ በማር፣ በዶሮ እርባታ፣ በሥጋ እንዲሁም በጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት ላይ ትኩረት በማድረግ የቤተሰብ ገቢን ለማሳደግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል።

በወገራ ወረዳ አምባ ጊዮርጊስ ከተማ በዶሮ እርባታ ሥራ የተሰማሩት አቶ አበራ ምስጋናው ለኢዜአ እንዳስታወቁት፤ በሌማት ትሩፋት መርሃ-ግብር በመታቀፍ በ1 ሺህ ጫጩቶች የጀመሩትን ሥራ በርትተው በመስራት የተሻለ ገቢ ማግኘት ጀምረዋል።


ሥራቸውን በማስፋፋትም አሁን ላይ በአንድ ጊዜ እስከ 3 ሺህ የሚደርሱ ዶሮዎችን አሳድገው ለመሸጥ የሚያስችል አቅም መፍጠራቸውን ተናግረዋል።

ሌላው የከተማዋ የ02 ቀበሌ ነዋሪ አቶ ማርየ ራራ በበኩላቸው፤ ከመንግሥት ሥራቸው ጎን ለጎን ባላቸው ትርፍ ጊዜ በሌማት ትሩፋት መርሃ-ግብር መሳተፋቸው የቤተሰባቸውን ሕይወት ከመለወጡ ባለፈ ተጨማሪ ሀብት ለመፍጠር እንደቻሉ ተናግረዋል።


አስተያየት ሰጪዎቹ በተሰማሩበት የዶሮ እርባታ ሥራ ውጤታማ እንዲሆኑ ከአካባቢው አስተዳደር የተደረገላቸው የቦታና የብድር ድጋፍ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አብራርተዋል።

የማዕከላዊ ጎንደር ዞን የእንስሳትና ዓሣ ሀብት ልማት መምሪያ ኃላፊ ዶክተር ምስጋናው ታከለ በበኩላቸው፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በሌማት ትሩፋት መርሃ-ግብር ብቻ ለ20 ሺህ 588 ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠር መቻሉን ተናግረዋል።


ዘርፉ ሥርዓተ-ምግብን ከማሻሻል ባለፈ ዜጎች የኑሮ ሁኔታቸውን እንዲለውጡና ሀብት እንዲፈጥሩ ማስቻሉንም አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026

በዞኑ የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ አጠናቆ ወደ ስራ ለማሰገባት አስችሏል

አምቦ፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እን...

Jul 24, 2026

 በዞኑ እየተካሔደ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል

ጎንደር፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ጎንደር ዞን የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ...

Jul 23, 2026