የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በደብረ ብርሃን ከተማ የሚገነባው የደረቅ ወደብ ተርሚናል የኢንዱስትሪና የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴን ለማሳለጥ ወሳኝ ሚና አለው

Aug 25, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደብረ ብርሃን፤ነሐሴ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል ደብረ ብርሃን ከተማ የሚገነባው የደረቅ ወደብ ተርሚናል በክልሉ በፍጥነት እያደገ የመጣውን የኢንዱስትሪና የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ለማሳለጥ ወሳኝ ሚና እንዳለው ተገለጸ።

በጠቅላላው 275 ሚሊዮን ብር ወጪ በደብረ ብርሀን ከተማ ለሚገነባው የደረቅ ወደብ ተርሚናል ዛሬ የመሰረት ድንጋይ በማስቀመጥ የግንባታ ሥራው በይፋ ተጀምሯል።


በማስጀመሪያ መርሀግብሩ ላይ የአማራ ክልል መንገድ፣ ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ቢሮ ሃላፊ ጋሻው አወቀ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ የደረቅ ወደብ ግንባታው በክልሉ በፍጥነት እያደገ የመጣውን የኢንዱስትሪና የኢንቨስትመንት ሥራዎች ለማሳለጥ ያግዛል።

በቢሮው ባለቤትነት ዛሬ የመሰረት ድንጋይ ተቀምጦ የግንባታ ሥራው የተጀመረው የደረቅ ወደብ ሲጠናቀቅ የደብረ ብርሀን ከተማና የማህበረሰቡን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ያሳድጋል ብለዋል።


ደብረ ብርሃን ከተማ ከጅቡቲ ወደብ እና ከአዲስ አበባ ከተማ ባላት ቅርበት ምክንያት ምርትን በፍጥነት ከውጪ ወደሀገር ውስጥ ለማስገባትና ለማስወጣት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳላት ገልጸዋል።

የወደቡ መገንባትም ተመራጭነቷን ይበልጥ ያሳድገዋል ብለዋል።


እንደ ሃላፊው ገለጻ የደረቅ ወደቡ ግንባታ ሥራ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ሲጠናቀቅ በቀን ከ1ሺህ በላይ የጭነት ተሽከርካሪዎችን የማስተናገድ አቅም ይኖረዋል።

የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ በድሉ ውብሸት በበኩላቸው እንዳሉት፣ ከከተማው ፈጣን እድገት ጋር ተያይዞ የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪዎች ቁጥር ከጊዜ ወደጊዜ እያደገ ነው።


ለዚህም የደረቅ ወደብ ተርሚናሉ መገንባት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው፤ ግንባታው በታቀደለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ ከተማ አስተዳደሩ አስፈላጊው እገዛና ትብብር ያደርጋል ብለዋል።

በተያያዘ ዜና የሰሜን ሸዋ ዞን መንገድ ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ መምሪያ ከ75 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጭ ያስገነባው የአሽከርካሪና ተሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ አገልግሎት ማዕከል ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል።


በተርሚናል ግንባታ ሥራ ማስጀመሪያ ላይ ከክልሉ፣ ከዞንና ከደብረብርሃን ከተማ አስተዳደር የተውጣጡ የሥራ ሀላፊዎችና የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍል ተወካዮች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026