የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ከምስራቅ ቦረና ዞን ቆላማ ወረዳዎች ከዘንድሮ የበልግ አዝመራ ከ2 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ተሰብስቧል

Sep 3, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ነገሌ ቦረና፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ቦረና ዞን ከዘንድሮው የበልግ አዝመራ ከ2 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ፡፡

በምስራቅ ቦረና ዞን ግብርና ጽህፈት ቤት የአዝርእት ልማትና ጥበቃ ባለሙያ አቶ ቦነያ ሁቃ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ ከ176 ሺህ 20 ሄክታር በላይ መሬት በበልግ አዝመራው በተለያዩ ሰብሎች መልማቱን አስታውሰዋል፡፡

በልማቱ ከተሳተፉት 143 ሺህ 288 ከፊል አርብቶ አደሮች መካከል 23 ሺህ 614 ሴቶች እንደሆኑ ገልጸዋል፡፡

በዞኑ ቆላማ ወረዳዎች ከለማው ከዚሁ መሬት 2 ሚሊዮን 126 ሺህ ኩንታል የሚጠጋ አጠቃላይ ምርት መሰብሰቡን አስታውቀዋል፡፡

በዞኑ የበልግ አዝመራ ከተመረቱት የሰብል አይነቶች መካከል ስንዴ፣ ጤፍ፣ በቆሎ፣ ቦለቄ፣ ማሽላና ሰሊጥ ዋና ዋናዎቹ እንደሆኑ ጠቁመዋል፡፡

ዘንድሮ ከዞኑ ሁሉም ወረዳዎች ከበልግ አዝመራ የተሰበሰበው አጠቃላይ ምርት ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር ብልጫ ያለው ነው ብለዋል፡፡

በበልግ አዝመራው ልማት ከተሳተፉት የዞኑ ነዋሪዎች መካከል የነገሌ ቦረና ከተማ ዙሪያ ወረዳ ነዋሪ አቶ አበራ ሞገስ ከበልግ አዝመራ ካለፉት አመታት ሁሉ የተሻለ ምርት መሰብሰባቸውን ገልጸዋል፡፡

የተሻሻለ የግብርና አሰራር፣ የምርት ማሳደጊያ አጠቃቀምና የተስተካከለ የዝናብ ስርጭት መኖሩ ውጤት ማስገኘቱን ጠቅሰዋል፡፡

የኩታ ገጠም አስተራረስ፣ በመስመር መዝራትና ሜካናይዜሽን አጠቃቀም ከተሻሸሉ የግብርና አሰራሮች መካከል ዋና ዋናዎቹ እንደሆኑም ለአብነት ጠቅሰዋል፡፡

በምስራቅ ቦረና ዞን ከመጋቢት አጋማሽ እስከ ሚያዝያ ወር የዝናብና የዘር፣ ከሐምሌ እስከ ነሔሴ ወር ደግሞ የምርት መሰብሰቢያ ወቅት እንደሆነ ይታወቃል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026