የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በኦሮሚያ ክልል ከመኸር ሰብል የተሻለ ምርት ለማግኘት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ

Sep 3, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ከ2018/19 የመኸር ሰብል የሚጠበቀውን ምርት ለማግኘት የሚያስችሉ የሰብል እንክብካቤ ሥራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

በተያዘው የምርት ወቅት የታቀደውን የምርት መጠን ለማሳካት የእርሻ መሬትን በአግባቡ አዘጋጅቶና ግብአቶችን ተጠቅሞ በዘር ከመሸፈን በመቀጠል ሰብሉን ከአረም፣ ከነፍሳትና ከተለያዩ በሽታዎች መከላከል ወሳኝ ነው።

የክልሉ ግብርና ቢሮ ከዚህ አኳያ አርሶ አደሩን ዘመናዊና ባህላዊ የሰብል ጥበቃ ዘዴዎችን አቀናጅቶ እንዲጠቀም ባለሙያዎችን መድቦ ድጋፍ በማድረግ ላይ ይገኛል።

የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌቱ ገመቹ ለኢዜአ እንደገለጹት በክልሉ ከመኸር አዝመራ የተሻለ ምርት በመሰብሰብ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ ይገኛል።


በክልሉ በምርት ዘመኑ ከ11 ነጥብ 1 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬትን በተለያዩ ሰብሎች በማልማት ከ380 ሚሊዮን 6 መቶ ሺህ ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን ተናግረዋል።

ከዚህ ውስጥም እስካሁን 9 ሚሊዮን 627 ሺህ 749 ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብሎች መሸፈኑን ገልጸዋል።

ምርታማነትን ለመጨመር የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ማሳደግ መቻሉን የጠቆሙት ኃላፊው፤ በዚህም 5 ሚሊዮን 158 ሺህ 516 ሄክታር የሚሆነው መሬት በትራክተር መታረሱን አስረድተዋል።

ከግብዓት አቅርቦት አንጻርም ከቀረበው ከ10 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ውስጥ እስካሁን ከ7 ሚሊዮን 677 ሺህ ኩንታል በላይ ለአርሶ አደሩ መሰራጨቱን አስታውቀዋል።

አቶ ጌቱ እንደተናገሩት የታቀደውን ምርት ለማሳካት በተለይም የተቀናጀ የሰብል እንክብካቤና ጥበቃ ሥራ በትኩረት እየተከናወነ ይገኛል።

አርሶ አደሩ ማሳቸውን በየጊዜው በመከታተልና በመፈተሽ የበሽታና የአረም ቁጥጥር ሥራዎችን በልዩ ትኩረት እያከናወነ እንደሚገኝም ገልጸዋል።

እንዲሁም አርሶ አደሩ በደቦ ባህላዊ የመረዳዳት ስልት በመጠቀም የኩትኳቶና አረም የመንቀል ተግባርን በሰፊው እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

የሰብል እንክብካቤና ጥበቃ ስራውን ለማጠናከርም የአረም እና ተባይ ማጥፊያ ኬሚካሎች ለአርሶ አደሩ እንዲሰራጩ መደረጉን ኃላፊው ገልጸዋል።

በዚህም በተቀናጀና በተናበበ አሰራር በተከናወኑ ስራዎች በአሁኑ ወቅት የሰብሉ ቁመና በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026

በዞኑ የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ አጠናቆ ወደ ስራ ለማሰገባት አስችሏል

አምቦ፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እን...

Jul 24, 2026