የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

መተግበሪያው የኢትዮጵያ 2030 የዲጂታል ጉዞ ግቦች ዕውን እንዲሆኑ የራሱን አስተዋጽኦ ያበረክታል- ኢንጂነር ታከለ ኡማ

Sep 7, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 29/2018 (ኢዜአ)፡-የዲጂታል መተግበሪያው መጀመር የኢትዮጵያ 2030 የዲጂታል ጉዞ ግቦች ዕውን እንዲሆኑ የራሱን አስተዋጽኦ የሚያበረክትበት ምዕራፍ መሆኑን የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ቦርድ አባል እና የኢትዮ-ጂቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማህበር ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ታከለ ኡማ ገለጹ።

የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ደንበኞች በዘመናዊ ዲጂታል አማራጭ የሚገለገሉበት የዲጂታል መተግበሪያ ዛሬ አስመረቋል።


የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ የቦርድ አባልና የኢትዮ-ጂቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማህበር ዋና ስራ አስፈጻሚ ታከለ ኡማ (ኢ/ር) ፤ ዛሬ የሚጀምረው ቴክኖሎጂ ትልቅ ትርጉም ያለውና ደንበኞች የተሻለ እንዲሁም ውጤታማ አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችል መሆኑን አመልክተዋል።

መንግስት የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ የምስራቅ አፍሪካ ትልቅ ተቋም እንዲሆን እንደሚፈልግ አንስተዋል።

ይህንንም ለማስቻል በርካታ ውጤታማ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።

ይፋ የተደረገው የዲጂታል አገልግሎት የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ጉዞን ለማሳካት የተያዙ ግቦች ዕውን እንዲሆኑ የራሱን ሚና የሚወጣበት ምዕራፍ መሆኑን ገልጸዋል።


የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዋና ስራ አስፈጻሚ አብዱልበር ሸምሱ (ኢ/ር) በበኩላቸው፤ ድርጅቱ እያደገ ያለውን ኢኮኖሚ የሚመጥን አገልግሎት ለመስጠት አሰራሩን እያዘመነ ይገኛል።

አገልግሎት አሰጣጡን ፈጣን፣ ቀልጣፋና ተደራሽነት ለማረጋገጥ በዲጂታል ቴክኖሎጂ ላይ ትኩረት ማድረጉን አስታውቀዋል።

ዛሬ የተመረቀው የዲጂታል መተግበሪያ የአገልግሎት አሰጣጡን የበለጠ በማዘመን ለደንበኞች ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት እንደሚያስችል ገልጸዋል።

ደንበኞች በመተግበሪያው አማካኝነት በሞባይል ስልካቸው እንዲመዘገቡ፣ የሂደት ክትትል እንዲያደርጉ እና ተያያዥ አገልግሎቶችን በፍጥነትና በምቾት እንዲያገኙ ያስችላል ብለዋል።

በቀጣይም በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ለማድረግና ውጤታማ አገልግሎት ለመስጠት የዲጂታል ቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባር እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026