የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የእመርታ ቀን ኢትዮጵያ ወደ አምራችነትና ራስን ወደ መቻል የምታደርገው መዋቅራዊ ሽግግር እየተበሰረ ነው

Sep 7, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ጳጉሜን 1/2018 ዓ.ም (ኢዜአ)፦ ጳጉሜን 1 የእመርታ ቀን ኢትዮጵያ ከተረጅነትና ከልመና አስተሳሰብ ወደ አምራችነትና ራስን ወደ መቻል የምታደርገውን መዋቅራዊ ሽግግር እያበሰረች መሆኑን የሚያሳይ ነው ሲሉ የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ (ዶ/ር) ገለጹ።

ዛሬ ጳጉሜን 1 ቀን 2018 ዓ.ም "እመርታ ለኢትዮጵያ ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል "የእመርታ ቀን" በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ይገኛል።

በመርሐ ግብሩ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የአጋር ድርጅቶች እና የግሉ ዘርፍ ተወካዮች ተገኝተዋል።


የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ የእመርታ ቀን አከባበር ኢትዮጵያ ከተረጅነት፣ ከጥገኝነት እና ከልመና አስተሳሰብ ተላቃ ወደ አምራችነትና ራስን ወደ መቻል የምታደርገውን መዋቅራዊና ታሪካዊ ሽግግር የሚያበስር ነው።

ሀገሪቷ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ያላትን አቅም በመጠቀም ያከናወነቻቸውን ዓበይት ተግባራትና ያስመዘገበቻቸውን ሁለንተናዊ ስኬቶች ለማሳየት ያለመ መሆኑንም ገልጸዋል።

በተለይም የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ስኬቶች፣ የግብርና ምርታማነትን በማረጋገጥ ረገድ የተመዘገቡ ድሎች፣ ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ እና በማዕድኑ ዘርፍ የታዩ ዓበይት እመርታዎች የዚሁ ታሪካዊ ሽግግር አካል መሆናቸውን ጠቁመዋል።

ማንሰራራት ማለት ያለፈው ታሪካችን የነበሩትን መልካም እሴቶች ይዞ፣ የነበሩብንን እክሎች በማስተካከልና በዘመናዊ እውቀትና ቴክኖሎጂ በመታገዝ ወደ አዲሱ የከፍታ ምዕራፍ መራመድ ነው ብለዋል።

የእመርታ ቀን "እመርታ ለኢትዮጵያ ማንሰራራት" በሚል ስናከብር ለኢትዮጵያ ብልፅግና እና ለአዲሱ መንግሥት የልማት አጀንዳዎች ትልቅ ግብዓት እንደሚሆኑ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026