የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በመዲናዋ ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የግብርና ምርቶች ቀርበዋል

Sep 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የግብርና ምርቶች አቅርቦት መዘጋጀቱን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአርሶ አደርና ከተማ ግብርና ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

ለመጪው የ2019 አዲስ ዓመት በዓል የሚቀርቡ የግብርና ምርቶች ጥራት እና ደህንነት ላይ የቁጥጥር ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑንም ኮሚሽኑ አስታውቋል፡፡

የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር ፀጋ ለማ (ዶ/ር) በሰጡት መግለጫ፤ ከነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በተለያዩ የገበያ ባዛሮችና ማዕከላት ስጋ፣ ዶሮ እና እንቁላል በተመጣጣኝ ዋጋ እየቀረበ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

ከምርት ጥራትና ደህንነት አንጻር በከተማዋ በሚገኙ ሶስት የቄራ ድርጅቶች ውስጥ ከ40 በላይ ስጋ መርማሪ ሀኪሞች ተመድበው ቁጥጥር እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል።

በተጨማሪም የስጋ ደህንነትን ለማረጋገጥ ለስጋ ማጓጓዣ ተሽከርካሪዎች ልዩ የጥራት ደረጃ ተዘጋጅቶ ስርጭቱ እየተከናወነ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

በሌላ በኩል፣ የወተት ምርት ጥራትና ደህንነትን ከመጠበቅ እስከ ስርጭት ባሉ ሂደቶች ተገቢውን ቁጥጥር ማድረግ የሚያስችል የአቅም ግንባታ ስራዎች መሰራታቸውን እና የጥራት መፈተሻ መሳሪያዎች እየተሟሉ መሆናቸውን አስታውቀዋል።

ሕብረተሰቡ በበዓል ወቅት በሚያከናውነው ግብይትና የቅርጫ እርድ ወቅት ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርግም ምክትል ኮሚሽነሩ አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026