የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ማረጋገጥ ብሔራዊ ጥቅም የማስጠበቅና የኢኮኖሚ ሉዓላዊነት ጉዳይ ነው

Sep 18, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መስከረም 7/2019 (ኢዜአ):- የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ማስመለስ ብሔራዊ ጥቅምን የማስጠበቅ፣ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን የማረጋገጥና ቀጣናዊ ሰላምን የማጠናከር ጉዳይ መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትሩ የወጣቶችና ስፖርት አማካሪ ሚኒስትር ቀጀላ መርዳሳ ገለጹ።

የአዲስ አበባ አመራር አካዳሚ የዓባይ ወንዝና የባሕር በር ጉዳይን በተመለከተ የፓናል ውይይት እያካሄደ ይገኛል።

የጠቅላይ ሚኒስትሩ የወጣቶችና ስፖርት አማካሪ ሚኒስትር ቀጀላ መርዳሳ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የባሕር በር ከኢትዮጵያ የኢኮኖሚ፣ የጸጥታ፣ የኃይል አቅርቦትና የንግድ ትስስር ጋር የተቆራኘ ነው።


ቀይ ባሕር ከዓለም አቀፍ የንግድና የኃይል ማጓጓዣ መስመሮች ጋር የተሳሰረ መሆኑን ገልጸው፤ ለኢትዮጵያ የንግድ ተደራሽነት፣ የሎጂስቲክስ አቅም፣ የኢኮኖሚ ተወዳዳሪነትና ጸጥታ ወሳኝ ሚና አለው ብለዋል።

ለኢትዮጵያ የባሕር በር ብሔራዊ ጥቅም የማስጠበቅ፣ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትና የቀጣናውን ሰላም የማረጋገጥ ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል።

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል አምባሳደር ዲና ሙፍቲ፤ የባሕር በር ከኢትዮጵያ ታሪክ፣ ጂኦግራፊ፣ ኢኮኖሚና የጸጥታ ሁኔታ ጋር የተያያዘ ዘላቂ ሀገራዊ አጀንዳ መሆኑን ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ ከቀይ ባሕር ጋር ያላት የጂኦግራፊ ቅርበት፣ የሕዝብ ቁጥሯና እያደገ የመጣው ኢኮኖሚ የባሕር በር አስፈላጊነት የጎላ ያደርገዋል ብለዋል።

ከሀገራዊ ጥቅም ባሻገር ከጎረቤትና ከቀሪው የአፍሪካ ሀገራት ብሎም ከዓለም አቀፍ ሥርዓት ጋር የሚኖረውን የኢኮኖሚና የጸጥታ ትስስር ማጤን እንደሚገባ ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ የባሕር በርን ጉዳይ በሰላማዊና በዲፕሎማሲያዊ መንገድ፣ በስምምነትና በትብብር መፍትሔ እንዲያገኝ አጥብቃ ትሻለች ብለዋል።

የአዲስ አበባ አመራር አካዳሚ ፕሬዝዳንት ጣሰው ገብሬ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ የባሕር በርና የዓባይ ጉዳዮች ከኢትዮጵያና ከአካባቢው የወደፊት የኢኮኖሚ፣ የደህንነትና የትስስር ጥቅሞች አንፃር ተመዝኖ መመራት እንዳለበት ገልጸዋል።

የባሕር በርና የዓባይ ጉዳዮች በውይይት፣ በመተማመን፣ በሕጋዊ ማዕቀፎችና የሁሉንም ሕዝቦች ዘላቂ የጋራ ጥቅም ታሳቢ በማድረግ መመራት አለባቸው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ማረጋገጥ ብሔራዊ ጥቅም የማስጠበቅና የኢኮኖሚ ሉዓላዊነት ጉዳይ ነው

አዲስ አበባ፤ መስከረም 7/2019 (ኢዜአ):- የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ማስመለስ ብሔራዊ ጥቅምን የማስጠበቅ፣ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን የማረጋገጥና ቀ...

Sep 18, 2026

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026