🔇Unmute
ጋምቤላ ፤ መስከረም 7/2019 (ኢዜአ)፦ የጋምቤላ ክልል ከተሞችን ለኑሮና ለኢንቨስትመንት ምቹ ለማድረግ የተጀመሩ ጥረቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር) ገለጹ።
የክልሉ የከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና የአዲሱ በጀት ዓመት እቅድ ላይ ያዘጋጀውን የውይይት መድረክ ዛሬ አካሄዷል።

የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የክልሉ ከተሞችን ለኑሮና ለኢንቨስትመንት ምቹ ለማድረግ የተጀመሩ ጥረቶች ተጠናክረው ይቀጥላሉ።
ከተሞችን ለነዋሪዎችና ለኢንቨስትመንት ምቹ ለማድረግ የመሠረተ ልማት ማስፋፋት ላይ የተጀመረው ጥረት እንደሚጠናከርም ገልጸዋል።
ለዚህም የኮሪደር ልማትን ጨምሮ የንጹህ መጠጥ ውሃ፣ የውስጥ ለውስጥ መንገድና ሌሎች የመሰረተ ልማት አውታሮችን ተደራሽ በማድረግ የህዝቡን የመሰረተ ልማት ጥያቄ ለመመለስ ትኩረት ተሰጥቷል ብለዋል።
ህብረተሰቡ ለከተሞች የመሰረተ ልማት ግንባታ፣ ጽዳትና ውበት ስራዎች መሳካትም እያደረገ ያለውን ሁለንተናዊ ተሳትፎና የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አጠናክሮ እንዲያስቀጥልም ጥሪ አቅርበዋል።

በበጀት ዓመቱ የተያዙ ፕሮጀክቶች በተቀመጠላቸው የጊዜ ሰሌዳ ተጠናቀው ለሕዝብ አገልግሎት እንዲበቁም የክትትልና ድጋፍ ስራዎች ይጠናከራሉ ብለዋል።
የመድረኩ ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት በከተሞች የሚታዩ የመጠጥ ውሃ፣ የውስጥ ለውስጥ መንገድና የፍሳሽ ማስወገጃ መስመር ተግዳሮቶችን ለመፍታት በትኩረት መስራት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
በግምገማ መድረኩ ላይ ከክልል፣ ከዞን፣ ከወረዳዎችና ከከተማ አስተዳደሮች የተውጣጡ የስራ ኃላፊዎችን ጨምሮ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
አዲስ አበባ፤ መስከረም 7/2019 (ኢዜአ):- የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ማስመለስ ብሔራዊ ጥቅምን የማስጠበቅ፣ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን የማረጋገጥና ቀ...
Sep 18, 2026
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026