አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 25/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ የመከላከያን ክብር በልህቀት በማረጋገጥ ከኢትዮጵያ አልፎ በአፍሪካ ተጽእኖ ፈጣሪ ተቋም ለመሆን እየሰራ እንደሚገኝ የዩኒቨርሲቲው ኮማንዳንት ብርጋዲየር ጀኔራል ከበደ ረጋሣ ገለጹ።
የኢትዮ ቴሌኮም አመራሮች የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲን ጎብኝተዋል።
አመራሮቹ በዩኒቨርሲቲው እየተሰጡ የሚገኙ የትምህርት ፕሮግራሞች፣ የጥናትና የምርምር ውጤቶች፣ የአይሲቲ መሰረተ ልማቶችና ሌሎች ስራዎችን ተመልክተዋል።
የዩኒቨርሲቲው ኮማንዳንት ብርጋዲየር ጀኔራል ከበደ ረጋሣ ዩኒቨርሲቲው ኢትዮጵያን ሌትና ቀን በጀግንነት እየጠበቀ የሚገኘው የሀገር መከላከያ ሰራዊትን በቴክኖሎጂ እውቀት የበቃና የዘመነ ለማድረግ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
ዩኒቨርሲቲው የመከላከያን ክብር በልህቀት ማረጋገጥ በሚያስችል አግባብ በትምህርትና በምርምር የተሻለ ሆኖ ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ተደራሽ ማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት እያከናወነ ይገኛል ብለዋል።
ከኢትዮጵያ አልፎ በአፍሪካ ላይ ተፅዕኖ ፈጣሪ ተቋም ለመሆን እየሰራ መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል።
ኢትዮ ቴሌኮምን ጨምሮ ሌሎች ተቋማት የዩኒቨርሲቲውን የለውጥ ሂደትና ሙያተኞችን በእውቀትና በክህሎት ብቁ ለማድረግ እየተከናወነ ላለው ስራ ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።
የኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ቴክኖሎጂ ኦፊሰር አቶ ታሪኩ ደምሴ ተቋሙ የዩኒቨርሲቲውን የለውጥ ሂደት እና የመከላከያን የእውቅትና ቴክኖሎጂ አቅም የሚያሳድጉ ድጋፎችን እንደሚያደርግ አመልክተዋል።
ኢትዮ ቴሌኮም ከዩኒቨርሲቲው ጋር ልምድና እውቀትን ማጋራት ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች በትብብር እንደሚሰራ መግለጻቸውን ከመከላከያ ሰራዊት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025