የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ዩኒቨርሲቲው የመከላከያን ክብር በልህቀት በማረጋገጥ ከኢትዮጵያ አልፎ በአፍሪካ ተጽእኖ ፈጣሪ ተቋም ለመሆን እየሰራ ነው

Jan 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 25/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ የመከላከያን ክብር በልህቀት በማረጋገጥ ከኢትዮጵያ አልፎ በአፍሪካ ተጽእኖ ፈጣሪ ተቋም ለመሆን እየሰራ እንደሚገኝ የዩኒቨርሲቲው ኮማንዳንት ብርጋዲየር ጀኔራል ከበደ ረጋሣ ገለጹ።

የኢትዮ ቴሌኮም አመራሮች የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲን ጎብኝተዋል።

አመራሮቹ በዩኒቨርሲቲው እየተሰጡ የሚገኙ የትምህርት ፕሮግራሞች፣ የጥናትና የምርምር ውጤቶች፣ የአይሲቲ መሰረተ ልማቶችና ሌሎች ስራዎችን ተመልክተዋል።


የዩኒቨርሲቲው ኮማንዳንት ብርጋዲየር ጀኔራል ከበደ ረጋሣ ዩኒቨርሲቲው ኢትዮጵያን ሌትና ቀን በጀግንነት እየጠበቀ የሚገኘው የሀገር መከላከያ ሰራዊትን በቴክኖሎጂ እውቀት የበቃና የዘመነ ለማድረግ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ዩኒቨርሲቲው የመከላከያን ክብር በልህቀት ማረጋገጥ በሚያስችል አግባብ በትምህርትና በምርምር የተሻለ ሆኖ ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ተደራሽ ማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት እያከናወነ ይገኛል ብለዋል።

ከኢትዮጵያ አልፎ በአፍሪካ ላይ ተፅዕኖ ፈጣሪ ተቋም ለመሆን እየሰራ መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል።

ኢትዮ ቴሌኮምን ጨምሮ ሌሎች ተቋማት የዩኒቨርሲቲውን የለውጥ ሂደትና ሙያተኞችን በእውቀትና በክህሎት ብቁ ለማድረግ እየተከናወነ ላለው ስራ ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።


የኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ቴክኖሎጂ ኦፊሰር አቶ ታሪኩ ደምሴ ተቋሙ የዩኒቨርሲቲውን የለውጥ ሂደት እና የመከላከያን የእውቅትና ቴክኖሎጂ አቅም የሚያሳድጉ ድጋፎችን እንደሚያደርግ አመልክተዋል።

ኢትዮ ቴሌኮም ከዩኒቨርሲቲው ጋር ልምድና እውቀትን ማጋራት ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች በትብብር እንደሚሰራ መግለጻቸውን ከመከላከያ ሰራዊት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026