የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ዩኒቨርሲቲው የመከላከያን ክብር በልህቀት በማረጋገጥ ከኢትዮጵያ አልፎ በአፍሪካ ተጽእኖ ፈጣሪ ተቋም ለመሆን እየሰራ ነው

Jan 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 25/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ የመከላከያን ክብር በልህቀት በማረጋገጥ ከኢትዮጵያ አልፎ በአፍሪካ ተጽእኖ ፈጣሪ ተቋም ለመሆን እየሰራ እንደሚገኝ የዩኒቨርሲቲው ኮማንዳንት ብርጋዲየር ጀኔራል ከበደ ረጋሣ ገለጹ።

የኢትዮ ቴሌኮም አመራሮች የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲን ጎብኝተዋል።

አመራሮቹ በዩኒቨርሲቲው እየተሰጡ የሚገኙ የትምህርት ፕሮግራሞች፣ የጥናትና የምርምር ውጤቶች፣ የአይሲቲ መሰረተ ልማቶችና ሌሎች ስራዎችን ተመልክተዋል።


የዩኒቨርሲቲው ኮማንዳንት ብርጋዲየር ጀኔራል ከበደ ረጋሣ ዩኒቨርሲቲው ኢትዮጵያን ሌትና ቀን በጀግንነት እየጠበቀ የሚገኘው የሀገር መከላከያ ሰራዊትን በቴክኖሎጂ እውቀት የበቃና የዘመነ ለማድረግ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ዩኒቨርሲቲው የመከላከያን ክብር በልህቀት ማረጋገጥ በሚያስችል አግባብ በትምህርትና በምርምር የተሻለ ሆኖ ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ተደራሽ ማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት እያከናወነ ይገኛል ብለዋል።

ከኢትዮጵያ አልፎ በአፍሪካ ላይ ተፅዕኖ ፈጣሪ ተቋም ለመሆን እየሰራ መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል።

ኢትዮ ቴሌኮምን ጨምሮ ሌሎች ተቋማት የዩኒቨርሲቲውን የለውጥ ሂደትና ሙያተኞችን በእውቀትና በክህሎት ብቁ ለማድረግ እየተከናወነ ላለው ስራ ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።


የኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ቴክኖሎጂ ኦፊሰር አቶ ታሪኩ ደምሴ ተቋሙ የዩኒቨርሲቲውን የለውጥ ሂደት እና የመከላከያን የእውቅትና ቴክኖሎጂ አቅም የሚያሳድጉ ድጋፎችን እንደሚያደርግ አመልክተዋል።

ኢትዮ ቴሌኮም ከዩኒቨርሲቲው ጋር ልምድና እውቀትን ማጋራት ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች በትብብር እንደሚሰራ መግለጻቸውን ከመከላከያ ሰራዊት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026