የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

Feb 24, 2025

IDOPRESS

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለፁ።

ሚኒስትሯ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና የክልሉ ገጠር ቴክኖሎጂ ብዜትና ግብርና ሜካናይዜሽን ማስፋፊያ ኤጀንሲ የሥራ እንቅስቃሴን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን በተገኙበት ተመልክተዋል።

ሚኒስትሯ በወቅቱ እንደገለፁት ኮሌጆች የአካባቢውን ነባራዊ ሁኔታ ባገናዘበ መልኩ ችግር ፈቺ የፈጠራ ሥራ እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው።

የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በከተማዋ እየተከናወነ ለሚገኘው የኮሪደር ልማት ግብዓት እያመረተ መሆኑን መመልከታቸውን ጠቅስዋል።


“ኮሌጁ ማሽነሪዎችን በመጠቀም ሌሎች የፋብሪካ ውጤቶችን እያመረተ ነው” ያሉት ሚኒስትሯ፤ የኮሌጁ አሰልጣኞች በተግባር የሚያከናውኗቸው ሥራዎች ለሌሎችም ተሞክሮ እንደሚሆኑ አመልክተዋል።

የገጠር ቴክኖሎጂ ብዜትና ግብርና ሜካናይዜሽን ማስፋፊያ ኤጄንሲ የግብርና ማሽነሪዎችን በማምረት ግብርናን ለማዘመን የሚያግዙ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

የቴክኒክና ሙያ ተቋማት በስራ ፈጠራ የራሳቸውን ገቢ እንዲያመነጩ ለሚደረገው ሂደት የሚያጠናክር እንደሆነ ጠቁመዋል።

ተቋማት በቴክኖሎጂ የታገዙ እና ዘመን ተሻጋሪ ለማድረግ በፖሊሲ ደረጃ እየተሰራ መሆኑንም ሚኒስትሯ አክለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026