የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

Feb 24, 2025

IDOPRESS

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለፁ።

ሚኒስትሯ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና የክልሉ ገጠር ቴክኖሎጂ ብዜትና ግብርና ሜካናይዜሽን ማስፋፊያ ኤጀንሲ የሥራ እንቅስቃሴን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን በተገኙበት ተመልክተዋል።

ሚኒስትሯ በወቅቱ እንደገለፁት ኮሌጆች የአካባቢውን ነባራዊ ሁኔታ ባገናዘበ መልኩ ችግር ፈቺ የፈጠራ ሥራ እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው።

የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በከተማዋ እየተከናወነ ለሚገኘው የኮሪደር ልማት ግብዓት እያመረተ መሆኑን መመልከታቸውን ጠቅስዋል።


“ኮሌጁ ማሽነሪዎችን በመጠቀም ሌሎች የፋብሪካ ውጤቶችን እያመረተ ነው” ያሉት ሚኒስትሯ፤ የኮሌጁ አሰልጣኞች በተግባር የሚያከናውኗቸው ሥራዎች ለሌሎችም ተሞክሮ እንደሚሆኑ አመልክተዋል።

የገጠር ቴክኖሎጂ ብዜትና ግብርና ሜካናይዜሽን ማስፋፊያ ኤጄንሲ የግብርና ማሽነሪዎችን በማምረት ግብርናን ለማዘመን የሚያግዙ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

የቴክኒክና ሙያ ተቋማት በስራ ፈጠራ የራሳቸውን ገቢ እንዲያመነጩ ለሚደረገው ሂደት የሚያጠናክር እንደሆነ ጠቁመዋል።

ተቋማት በቴክኖሎጂ የታገዙ እና ዘመን ተሻጋሪ ለማድረግ በፖሊሲ ደረጃ እየተሰራ መሆኑንም ሚኒስትሯ አክለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026