
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለፁ።
ሚኒስትሯ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና የክልሉ ገጠር ቴክኖሎጂ ብዜትና ግብርና ሜካናይዜሽን ማስፋፊያ ኤጀንሲ የሥራ እንቅስቃሴን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን በተገኙበት ተመልክተዋል።
ሚኒስትሯ በወቅቱ እንደገለፁት ኮሌጆች የአካባቢውን ነባራዊ ሁኔታ ባገናዘበ መልኩ ችግር ፈቺ የፈጠራ ሥራ እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው።
የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በከተማዋ እየተከናወነ ለሚገኘው የኮሪደር ልማት ግብዓት እያመረተ መሆኑን መመልከታቸውን ጠቅስዋል።

“ኮሌጁ ማሽነሪዎችን በመጠቀም ሌሎች የፋብሪካ ውጤቶችን እያመረተ ነው” ያሉት ሚኒስትሯ፤ የኮሌጁ አሰልጣኞች በተግባር የሚያከናውኗቸው ሥራዎች ለሌሎችም ተሞክሮ እንደሚሆኑ አመልክተዋል።
የገጠር ቴክኖሎጂ ብዜትና ግብርና ሜካናይዜሽን ማስፋፊያ ኤጄንሲ የግብርና ማሽነሪዎችን በማምረት ግብርናን ለማዘመን የሚያግዙ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
የቴክኒክና ሙያ ተቋማት በስራ ፈጠራ የራሳቸውን ገቢ እንዲያመነጩ ለሚደረገው ሂደት የሚያጠናክር እንደሆነ ጠቁመዋል።
ተቋማት በቴክኖሎጂ የታገዙ እና ዘመን ተሻጋሪ ለማድረግ በፖሊሲ ደረጃ እየተሰራ መሆኑንም ሚኒስትሯ አክለዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026