
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለፁ።
ሚኒስትሯ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና የክልሉ ገጠር ቴክኖሎጂ ብዜትና ግብርና ሜካናይዜሽን ማስፋፊያ ኤጀንሲ የሥራ እንቅስቃሴን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን በተገኙበት ተመልክተዋል።
ሚኒስትሯ በወቅቱ እንደገለፁት ኮሌጆች የአካባቢውን ነባራዊ ሁኔታ ባገናዘበ መልኩ ችግር ፈቺ የፈጠራ ሥራ እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው።
የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በከተማዋ እየተከናወነ ለሚገኘው የኮሪደር ልማት ግብዓት እያመረተ መሆኑን መመልከታቸውን ጠቅስዋል።

“ኮሌጁ ማሽነሪዎችን በመጠቀም ሌሎች የፋብሪካ ውጤቶችን እያመረተ ነው” ያሉት ሚኒስትሯ፤ የኮሌጁ አሰልጣኞች በተግባር የሚያከናውኗቸው ሥራዎች ለሌሎችም ተሞክሮ እንደሚሆኑ አመልክተዋል።
የገጠር ቴክኖሎጂ ብዜትና ግብርና ሜካናይዜሽን ማስፋፊያ ኤጄንሲ የግብርና ማሽነሪዎችን በማምረት ግብርናን ለማዘመን የሚያግዙ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
የቴክኒክና ሙያ ተቋማት በስራ ፈጠራ የራሳቸውን ገቢ እንዲያመነጩ ለሚደረገው ሂደት የሚያጠናክር እንደሆነ ጠቁመዋል።
ተቋማት በቴክኖሎጂ የታገዙ እና ዘመን ተሻጋሪ ለማድረግ በፖሊሲ ደረጃ እየተሰራ መሆኑንም ሚኒስትሯ አክለዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026