የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

Feb 12, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ ኢኒሼቲቭ የወቅቱ ሊቀመንበርና የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ ተናገሩ።

የአፍሪካ ቀንድ ኢኒሼቲቭ በኢትዮጵያ የመጣውን ሪፎርምና የቀጣናውን ጠንካራ ግንኙነት ተከትሎ በቀጣናው አገራት የገንዘብ ሚኒስትሮች ጥቅምት 2012 ዓ.ም መመስረቱ ይታወቃል።

የኢኒሼቲቩ ሊቀመንበርና የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ ኢትዮጵያ በኢኒሼቲቩ አማካይነት ከጎረቤት ሀገራት ጋር የሚያስተሳስር የልማት ፕሮጀክቶች እየተገበረች መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ መንግስት ለቀጣናዊ ልማትና ኢኮኖሚያዊ ትስስር ቁርጠኝነት አቋም እንዳለውም ገልጸዋል።

በዚህም ሀገሪቱ ቀጣናውን በመንገድ፣ በባቡርና በሃይልና ሌሎች መሰረተ ልማቶች የሚያስተሳስሩ ድንበር ተሻጋሪ ልማቶችን በመሪነት እያከናወነች ነው ብለዋል።

እንደ ሚኒስትሩ ማብራሪያ ኢኒሼቲቩ ባለፉት አምስት ዓመታት ለተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች 15 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ፋይናንስ ከልማት አጋሮች ለመሰብሰብ አቅዶ ሲሰራ ቆይቷል።

በዚህም ከግማሽ በላይ የሚሆነው ፋይናንስ ከልማት አጋሮች የተገኘ ሲሆን፥ ለተለያዩ ፕሮጀክቶች ማስፈጸሚያ መዋሉን ጠቅሰዋል።

በዚህም ኢትዮጵያ በርካታ የልማት ፕሮጀክቶችን እየተገበረች ሲሆን ከ3 ቢሊዮን ዶላር በላይ የልማት ድጋፍ ማግኘቷን አንስተዋል።

በእነዚህ ፕሮጀክቶች ከተገኙ ውጤቶች መካከልም የድርቅ መረጃ ጠቋሚ መድህን በቆላማ አካባቢዎች በስፋት ተግባራዊ መደረጉን ተናግረዋል።

በአርብቶ አደር አካባቢዎች የተገነቡ የውሃ መሰረተ ልማቶች፣ ምርትና ምርታማነት ማሳደግን ጨምሮ 500 ሺህ ሔክታር መሬትን ከአንበጣ መንጋ ወረራ ማዳን መቻሉን ለአብነት አንስተዋል።

ኢኒቬቲቩ ኢትዮጵያ በየጊዜው እያስመዘገበች ያለው የኢኮኖሚ ዕድገትና የህዝብ ቁጥር መጨመርን ተከትሎ በቀጣናው የልማት ትስስር ላይ ግንባር ቀደም ሚናዋን አጠናክራ እንድትቀጥል ያግዛታል ብለዋል።

ሚኒስትሩ አክለውም በመጪው የካቲት 11 ቀን 2017 ዓ.ም 23ኛው የአፍሪካ ቀንድ አገራት የገንዘብ ሚኒስትሮችና የልማት አጋሮች የጋራ ስብሳባ በአዲስ አበባ እንደሚካሄድም ጠቁመዋል።

በስብሰባው ኢኒሼቲቩ ባለፉት አምስት ዓመታት ያከናወናቸው ስራዎች ላይ ግምገማ የሚካሄድ ሲሆን በቀጣይም ሊተገበሩ የሚችሉ ፕሮጀክቶች ላይ ውይይት ይደረጋል ብለዋል።

ኢትዮጵያን ኢኒሼቲቩን ላለፉት ሁለት ዓመታት በሊቀመንበርነት የመራች ሲሆን ከሚኒስትሮቹ ስብሰባ በኋላ የሊቀመንበርነት ስልጣኑን ለሌላ አባል ሀገር ታስረክባለች።

ኢኒሼቲቩ ኢትዮጵያን፣ ጅቡቲን ኤርትራን፣ ኬንያን፣ ሶማሊያን፣ ሱዳንንና ደቡብ ሱዳንን ያቀፈ ሲሆን ዋነኛ ዓላማውም በቀጣናው መሰረተ ልማት ትብብርን ማጎልበት፣ የንግድና ኢኮኖሚ ውህደትን ማጠናከር የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ችግሮችን የመቋቋም አቅም መገንባትና የሰው ሃይል ልማትን ማጠናከር ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026