የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

Feb 12, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ ኢኒሼቲቭ የወቅቱ ሊቀመንበርና የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ ተናገሩ።

የአፍሪካ ቀንድ ኢኒሼቲቭ በኢትዮጵያ የመጣውን ሪፎርምና የቀጣናውን ጠንካራ ግንኙነት ተከትሎ በቀጣናው አገራት የገንዘብ ሚኒስትሮች ጥቅምት 2012 ዓ.ም መመስረቱ ይታወቃል።

የኢኒሼቲቩ ሊቀመንበርና የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ ኢትዮጵያ በኢኒሼቲቩ አማካይነት ከጎረቤት ሀገራት ጋር የሚያስተሳስር የልማት ፕሮጀክቶች እየተገበረች መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ መንግስት ለቀጣናዊ ልማትና ኢኮኖሚያዊ ትስስር ቁርጠኝነት አቋም እንዳለውም ገልጸዋል።

በዚህም ሀገሪቱ ቀጣናውን በመንገድ፣ በባቡርና በሃይልና ሌሎች መሰረተ ልማቶች የሚያስተሳስሩ ድንበር ተሻጋሪ ልማቶችን በመሪነት እያከናወነች ነው ብለዋል።

እንደ ሚኒስትሩ ማብራሪያ ኢኒሼቲቩ ባለፉት አምስት ዓመታት ለተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች 15 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ፋይናንስ ከልማት አጋሮች ለመሰብሰብ አቅዶ ሲሰራ ቆይቷል።

በዚህም ከግማሽ በላይ የሚሆነው ፋይናንስ ከልማት አጋሮች የተገኘ ሲሆን፥ ለተለያዩ ፕሮጀክቶች ማስፈጸሚያ መዋሉን ጠቅሰዋል።

በዚህም ኢትዮጵያ በርካታ የልማት ፕሮጀክቶችን እየተገበረች ሲሆን ከ3 ቢሊዮን ዶላር በላይ የልማት ድጋፍ ማግኘቷን አንስተዋል።

በእነዚህ ፕሮጀክቶች ከተገኙ ውጤቶች መካከልም የድርቅ መረጃ ጠቋሚ መድህን በቆላማ አካባቢዎች በስፋት ተግባራዊ መደረጉን ተናግረዋል።

በአርብቶ አደር አካባቢዎች የተገነቡ የውሃ መሰረተ ልማቶች፣ ምርትና ምርታማነት ማሳደግን ጨምሮ 500 ሺህ ሔክታር መሬትን ከአንበጣ መንጋ ወረራ ማዳን መቻሉን ለአብነት አንስተዋል።

ኢኒቬቲቩ ኢትዮጵያ በየጊዜው እያስመዘገበች ያለው የኢኮኖሚ ዕድገትና የህዝብ ቁጥር መጨመርን ተከትሎ በቀጣናው የልማት ትስስር ላይ ግንባር ቀደም ሚናዋን አጠናክራ እንድትቀጥል ያግዛታል ብለዋል።

ሚኒስትሩ አክለውም በመጪው የካቲት 11 ቀን 2017 ዓ.ም 23ኛው የአፍሪካ ቀንድ አገራት የገንዘብ ሚኒስትሮችና የልማት አጋሮች የጋራ ስብሳባ በአዲስ አበባ እንደሚካሄድም ጠቁመዋል።

በስብሰባው ኢኒሼቲቩ ባለፉት አምስት ዓመታት ያከናወናቸው ስራዎች ላይ ግምገማ የሚካሄድ ሲሆን በቀጣይም ሊተገበሩ የሚችሉ ፕሮጀክቶች ላይ ውይይት ይደረጋል ብለዋል።

ኢትዮጵያን ኢኒሼቲቩን ላለፉት ሁለት ዓመታት በሊቀመንበርነት የመራች ሲሆን ከሚኒስትሮቹ ስብሰባ በኋላ የሊቀመንበርነት ስልጣኑን ለሌላ አባል ሀገር ታስረክባለች።

ኢኒሼቲቩ ኢትዮጵያን፣ ጅቡቲን ኤርትራን፣ ኬንያን፣ ሶማሊያን፣ ሱዳንንና ደቡብ ሱዳንን ያቀፈ ሲሆን ዋነኛ ዓላማውም በቀጣናው መሰረተ ልማት ትብብርን ማጎልበት፣ የንግድና ኢኮኖሚ ውህደትን ማጠናከር የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ችግሮችን የመቋቋም አቅም መገንባትና የሰው ሃይል ልማትን ማጠናከር ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026