
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለጹ፡፡
የደቡብ ወሎ ዞን ከፍተኛ አመራር አባላት በዞኑ ተሁለደሬ ወረዳ በበጋ መስኖ የለማውን የስንዴ ሰብል ዛሬ ጎብኝተዋል፡፡
የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን በጉብኝቱ ላይ እንደገለጹት ዞኑ ለስንዴ ልማት ምቹ በመሆኑ ምርታማነትን በማሳደግ በምግብ ራስን ለመቻል እየተሰራ ነው፡፡
ለዚህም በቴክኖሎጂ ታግዘው የተሻሻሉ የግብርና አሰራሮችን በማስፋት የበጋ መስኖ ስንዴ ልማቱን ውጤታማ ለማድረግ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ካለፉት ዓመታት ልምድና ተሞክሮ በመውሰድ ዘንድሮ የተሻለ ውጤት መመዝገቡን የተናገሩት ዋና አስተዳዳሪው፤ የግብዓት አቅርቦቱም የተሻለ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
''ቀደም ሲል ለምተው የማያውቁና ፆም ያድሩ የነበሩ አካባቢዎችን ጭምር በማልማት ምርታማነትን እያሳደግን እንገኛለን'' ብለዋል፡፡
የደቡብ ወሎ ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አህመድ ጋሎ በበኩላቸው በቂ ግብዓት ለአርሶ አደሩ ማቅረብ በመቻሉ ከ20 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በበጋ መስኖ ስንዴ ማልማት ተችሏል ብለዋል፡፡
ለበጋ መስኖ ልማት ስራው ከ27 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ጥቅም ላይ መዋሉን ጠቁመው፤ ተገቢውን የሰብል እንክብካቤ በማድረግ፣ ከአረምና ከተባይ መከላከል መቻሉን ተናግረዋል።
በበጋ መስኖ ከለማው መሬትም ከ800 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት ይጠበቃል ብለዋል፡፡
''አሁን ላይ በሁሉም ወረዳዎች የስንዴ ሰብል ቁመና በጥሩ ሁኔታ ላይ ይገኛል'' ያሉት አቶ አህመድ፤ አርሶ አደሩ በየቀኑ ማሳውን በማሰስና ሰብሉን በመንከባከብ ምርታማነቱን ማሳደግ እንዲችል ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ከአርሶ አደሩ ጋር በመግባባት በወረዳው ከ2 ሺህ 500 ሄክታር መሬት በላይ በበጋ መስኖ ስንዴ ማልማት መቻሉን የተናገሩት ደግሞ የተሁለደሬ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኡስማን ካሳው ናቸው፡፡
አርሶ አደሩም ጠቀሜታውን በውል ተረድቶ በራሱ ተነሳሽነት ጭምር የመስኖ ስንዴን በማልማት በምግብ ራሱን ከመቻል ባለፈ ምርቱን በስፋት ለገበያ እያቀረበ ነው ብለዋል፡፡
በተሁለደሬ ወረዳ የ018 ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ዓሊ እንድሪስ በሰጡት አሰተያየት በዘንድሮው የበጋ ወቅት ግማሽ ሄክታር ማሳቸውን በበጋ መስኖ ስንዴ አልምተው የአረምና የተባይ ቁጥጥር ሥራ እያከናወኑ ነው፡፡
ከ20 ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት የተሻሻሉ አሰራሮችን በመከተል የሰብል እንክብካቤ እያደረጉ መሆናቸውንም ተናግረዋል፡፡
በጉብኝቱ ላይ የዞንና ወረዳ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026