የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በግብርናው ዘርፍ የሚደረጉ ጥናትና ምርምሮች ለውጤት እንዲበቁ የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ሊጠናከር ይገባል

Jan 13, 2025

IDOPRESS

ሆሳዕና፤ ታኅሣሥ 26/2017(ኢዜአ):- በግብርና ዘርፍ የሚከናወኑ የጥናትና ምርምር ስራዎች ለውጤት እንዲበቁ የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ እንዲጠናከር የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ጠየቀ።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርናው ዘርፍ ያሉ ዕድሎችንና ማነቆዎችን ለመለየት የተከናወኑ ጥናቶች ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ በሆሳዕና ከተማ ዛሬ ተካሄዷል።

በኢንስቲትዩቱ የምግብ ማጠናከሪያ ፕሮግራም የምርምር ዘርፍ ዳይሬክተር ንጉሴ ዳና (ዶ/ር) እንዳሉት ኢንስቲትዩቱ በስምንት የምርምር ማዕከላት የግብርናውን ዘርፍ የሚያግዙ የጥናትና ምርምር ውጤቶች እንዲፈልቁና ተደራሽ እንዲሆኑ እያደረገ ነው።

በተለይም ቴክኖሎጂን የማስረጽ ስራ ውጤት እየተገኘበት መሆኑን ጠቅሰው እነዚህን ጅምር ስራዎች በመደገፍ ረገድ ባለድርሻ አካላት መረባረብ አለባቸው ብለዋል።

ኢንስቲትዩቱ ለግብርናው ዘርፍ ማነቆ የሆኑ ችግሮችን መፍታት የሚያስችሉ የምርምር ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን የገለጹት ዳይሬክተሩ የቴክኖሎጂዎች አቅርቦትን በማመቻቸት፣ በማስፋትና በማስተዋወቅ ለተጠቃሚው እንዲደርስ የሁሉም ርብርብ ያስፈልጋል ብለዋል።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር በበኩላቸው በክልሉ በምርምር የተገኙ የግብርና ተክኖሎጂዎች ተደራሽነት ትኩረት ማግኘቱን ገልጸዋል።

የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ፣ የግብርና ምርቶችን በአይነትና በጥራት ማምረትና ዘርፉ ለዜጎች የስራ እድል መፍጠሪያ እንዲሆን ትኩረት ተሰጥቷል ብለዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ምርምር ኢንቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ፀጋዬ ተረፈ፣ በክልሉ የግብርና ልማትን የሚያግዙ የጥናትና ምርምር ስራዎች በትብብር እየተሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በዚህም በተቋሙ ስር የሚገኙ የምርምር ማዕከላትንና ንዑስ የምርምር ጣቢያዎችን በማቀናጀት በርካታ የጥናት ስራዎች መከናወናቸውን አስረድተዋል።

በመርሐ ግብሩ ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራር አባላት፣ የዞንና የልዩ ወረዳ ግብርና መምሪያ ኃላፊዎች፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አመራር አባላትና ሌሎች እንግዶች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026