
ሆሳዕና፤ ታኅሣሥ 26/2017(ኢዜአ):- በግብርና ዘርፍ የሚከናወኑ የጥናትና ምርምር ስራዎች ለውጤት እንዲበቁ የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ እንዲጠናከር የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ጠየቀ።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርናው ዘርፍ ያሉ ዕድሎችንና ማነቆዎችን ለመለየት የተከናወኑ ጥናቶች ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ በሆሳዕና ከተማ ዛሬ ተካሄዷል።
በኢንስቲትዩቱ የምግብ ማጠናከሪያ ፕሮግራም የምርምር ዘርፍ ዳይሬክተር ንጉሴ ዳና (ዶ/ር) እንዳሉት ኢንስቲትዩቱ በስምንት የምርምር ማዕከላት የግብርናውን ዘርፍ የሚያግዙ የጥናትና ምርምር ውጤቶች እንዲፈልቁና ተደራሽ እንዲሆኑ እያደረገ ነው።
በተለይም ቴክኖሎጂን የማስረጽ ስራ ውጤት እየተገኘበት መሆኑን ጠቅሰው እነዚህን ጅምር ስራዎች በመደገፍ ረገድ ባለድርሻ አካላት መረባረብ አለባቸው ብለዋል።
ኢንስቲትዩቱ ለግብርናው ዘርፍ ማነቆ የሆኑ ችግሮችን መፍታት የሚያስችሉ የምርምር ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን የገለጹት ዳይሬክተሩ የቴክኖሎጂዎች አቅርቦትን በማመቻቸት፣ በማስፋትና በማስተዋወቅ ለተጠቃሚው እንዲደርስ የሁሉም ርብርብ ያስፈልጋል ብለዋል።
በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር በበኩላቸው በክልሉ በምርምር የተገኙ የግብርና ተክኖሎጂዎች ተደራሽነት ትኩረት ማግኘቱን ገልጸዋል።
የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ፣ የግብርና ምርቶችን በአይነትና በጥራት ማምረትና ዘርፉ ለዜጎች የስራ እድል መፍጠሪያ እንዲሆን ትኩረት ተሰጥቷል ብለዋል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ምርምር ኢንቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ፀጋዬ ተረፈ፣ በክልሉ የግብርና ልማትን የሚያግዙ የጥናትና ምርምር ስራዎች በትብብር እየተሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በዚህም በተቋሙ ስር የሚገኙ የምርምር ማዕከላትንና ንዑስ የምርምር ጣቢያዎችን በማቀናጀት በርካታ የጥናት ስራዎች መከናወናቸውን አስረድተዋል።
በመርሐ ግብሩ ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራር አባላት፣ የዞንና የልዩ ወረዳ ግብርና መምሪያ ኃላፊዎች፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አመራር አባላትና ሌሎች እንግዶች ተሳትፈዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026