
አዲስ አበባ፤ ጥር 3/2017(ኢዜአ)፡- የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር በ3ኛው ዙር የሳይበር ታለንት ሰመር ካምፕ ፕሮግራም ያሰለጠናቸውን ሰልጣኞች አስመረቀ።
አስተዳደሩ የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ የቅዳሜና እሁድ የስልጠና ፕሮግራም ከተለያዩ ትምህርት ቤቶች ለተውጣጡ ተማሪዎች መስጠት ጀምሯል።
የሳይበር ታለንት ሰመር ካምፕ ስልጠናቸውን አጠናቀው ለምረቃ የበቁት ከመላ ኢትዮጵያ የተውጣጡ 237 ባለልዩ ተሰጥኦ ወጣቶች ናቸው።

የአስተዳደሩ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዳንኤል ጉታ በዚሁ ጊዜ፥ ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ብቃት ያለው የሳይበር ባለሙያ በብዛትና በጥራት ማፍራት ያስፈልጋል ብለዋል።
አስተዳደሩ ከመላ ኢትዮጵያ የተውጣጡ ባለልዩ ተሰጥኦ ታዳጊዎችን በሳይበርና ተያያዥ ጉዳዮች እያበቃ እንደሚገኝም ገልጸዋል።
ተለዋዋጭ የቴክኖሎጂ ዕድገትን የሚመጥንና የሳይበር ጥቃትን ለመከላከል ብቁና ተወዳዳሪ ባለሙያ የማፍራት ጥረቱ ይቀጥላል ብለዋል።
በአስተዳደሩ የሳይበር ማዕከል ዳይሬክተር ቢሻው በየነ በበኩላቸው ከሀገራዊ ለውጡ በኃላ ለባለተሰጥኦ ወጣቶች ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም ማዕከሉ ከሳይበር ደህንነት ጋር በተያያዘ የሚሰጠው ስልጠና ተደራሽነት እየጨመረ መምጣቱን ተናግረዋል።
ሰልጣኞቹ በበኩላቸው በስልጠናው መሰረታዊ የዲጂታል ዕውቀት ማግኘታቸውን ጠቅሰዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026