የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ለዩኒቨርሲቲ ኢንዱስትሪ ትስስር የተፈጠረውን ምቹ ዕድል በመጠቀም ለውጤታማነቱ በቅንጅት እንሰራለን - ዩኒቨርሲቲዎች

Jan 13, 2025

IDOPRESS

ሀዋሳ፤ጥር 4/2017 (ኢዜአ)፡-መንግስት ለዩኒቨርሲቲ ኢንዱስትሪ ትስስሩ የፈጠረውን ምቹ ዕድል በመጠቀም ለውጤታማነቱ በቅንጅት እንደሚሰሩ የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ገለጹ።

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና፣ የምርምር ተቋማትና የኢንዱስትሪዎች ትስስር አዋጅ (1298/2015) ከዚህ ቀደም በተጠናጥል የሚከናወኑ ሥራዎችን በቅንጅት ለመስራት የሚያስችል ነው።

ትምህርት ሚኒስቴርም አዋጁን መሰረት በማድረግ በአገሪቱ ያሉ ዩኒቨርሲቲዎች በአምስት ክላስተሮች ተደራጅተው በቅንጅት እንዲንቀሳቀሱ አቅጣጫ አስቀምጧል።

በደቡብ ቅርንጫፍ የተደራጁት ዘጠኝ ዩኒቨርሲቲዎች በአዋጁና በቀጣይ የስራ አቅጣጫዎች ላይ በሀዋሳ ዩኒቨርኒሲቲ መክረዋል።

በጉዳዩ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የዲላ፣ ጅማና ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲዎች መንግስት ለዩኒቨርሲቲ ኢንዱስትሪ ትስስሩ የፈጠረውን ምቹ ዕድል በመጠቀም ለውጤታማነቱ ተቀናጅተው እንደሚሰሩ ገልጸዋል።

በዲላ ዩኒቨርሲቲ የኢንዱስትሪ ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክተር አቶ አዲሱ ፊሬንጆ ዩኒቨርሲቲ ኢንዱስትሪ ትስስር በአዋጅ መደገፉና አገራዊ መዋቅር እንዲኖረው መደረጉ ቀደም ሲል የነበሩ ክፍተቶችን ለማረም የሚያስችል ነው።

ዩኒቨርሲቲው ከ20 ኢንዱስትሪዎች ጋር ትስስር በመፍጠር በምርምርና ስልጠና የተለያዩ ተግባራት እያከናወነ መሆኑን ጠቁመው፣ ዘንድሮም ከስምንት ተጨማሪ ኢንዱስትሪዎች ጋር በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት መፈራረሙን ተናግረዋል።

በአሁኑ ወቅት ለዩኒቨርሲቲ ኢንዱስትሪ ትስስር እንደአገር የተፈጠረው ምቹ ሁኔታ የትምህርት ተቋማቱ በቅንጅት እንዲሰሩ እድል ከመፍጠር ባለፈ አገራዊ አበርክቷቸውን ያሳድጋል ብለዋል።


የጅማ ዩኒቨርሲቲ ኢንዱስትሪ ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክተር ተፈራ መኮንን (ዶ/ር) በበኩላቸው አዲሱ አዋጅ የዩኒቨርሲቲ ኢንዱስትሪ ትስስሩን እንደሚያጠናክር ነው የገለጹት።

ጅማ ዩኒቨርሲቲ በግብርና፣ ጤናና ኮንስትራክሽን ዘርፍ ከሚሰሩ ኢንዱስትሪዎች ጋር በቅርበት እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው፣ አዋጁ እነዚህን የተጀመሩ ሥራዎች ከማጠናከር ባለፈ ዩኒቨርሲቲዎች በጋራ እንዲሰሩ የሚያደርግ ነው ብለዋል።

ሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ እና ይርጋለም የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርክን ጨምሮ ከተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ጋር በትብብር እየሰራ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ትብብር ምክትል ፕሬዚዳንት ታፈሰ ማቲዎስ (ዶ/ር) ናቸው።


በተፈጠው ትስስር ለኢንዱስትሪው ችግር ፈቺ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን መፍጠርና የምርምር ውጤቶችን ማቅረብ እንደተቻለ ጠቁመው፣ አዋጁ ትስስሩ ህጋዊ መሰረት እንዲኖረው የሚያደርግ ነው ብለዋል።

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው መስክ ምርታማነት የሚያሳድጉ ምርምሮችን የማድረግና አሲዳማ አፈርን የማከም ሥራ እያከናወነ መሆኑን የገለጹት ምክትል ፕሬዚዳንቱ፣ የክልሉን የኢንዱስትሪ ፍኖተ ካርታ ማጠናቀቁንም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ባለፉት አምስት ዓመታት አዲስ አበባን የሰላምና የልማት ማዕከል ማድረግ ተችሏል – ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 10/2018(ኢዜአ)፦ ባለፉት አምስት ዓመታት ስር የሰደዱ ችግሮችን በመቅረፍ አዲስ አበባን የሰላምና የልማት ማዕከል ማድረግ መቻሉን የአዲስ...

Jul 18, 2026

በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገበ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገ...

Jun 24, 2026

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026