የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝ ለማድረግ ለኔትወርክ ማሻሻያና መልሶ ግንባታ ስራ ትኩረት ተስጥቷል

Jan 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2017(ኢዜአ)፦የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝ ለማድረግ የኔትወርክ ማሻሻያና መልሶ ግንባታ ስራ በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ገለጸ።

መንግስት የአገሪቱን የኃይል አቅርቦት ከፍላጎቱ ጋር ለማመጣጠን በርካታ ተግባራት እያከናወነ ይገኛል።

በኢትዮጵያ የከተሜነት መስፋፋትና የሕዝብ ቁጥር በፍጥነት ማደጉን ተከትሎ የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎቱ በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ መጥቷል።

ለዚህም በታዳሽ ኃይል ላይ ትኩረት በማድረግ ከውኃ፣ ከንፋስ፣ ከእንፋሎትና ከፀሐይ በቂ ኃይል ለማመንጨት የሚያስችሉ ስራዎች በስፋት በመከናወን ላይ ናቸው።

በአጠቃላይ በመላ ሀገሪቱ አምስት ሚሊየን የሚጠጉ የህብረተሰብ ክፍሎች የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆናቸውን የአገልግሎቱ የኮሚኒኬሽን ስራ አስፈጻሚ አቶ መላኩ ታዬ ለኢዜአ ተናግረዋል።

በሀገር አቀፍ ደረጃ በከተሞችና የገጠር ቀበሌዎች የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚነትን ለማስፋት እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።

በኃይል ረገድ አዳዲስ ደንበኞችን ተደራሽ የማድረግና ከአሌክትሪክ መስመር ርቀው የሚገኙ አካባቢዎች ደግሞ ከፀሐይ ኃይል አማራጭ ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተደረገ ነው ብለዋል።

ለኤሌክትሪክ ተደራሽነት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ የተለያዩ የውኃ ኃይል ማመንጫዎች አገልግሎት እንዲሰጡ መንግስት በልዩ ትኩረት እየሰራ ስለመሆኑም ጠቅሰዋል።

አብዛኛዎቹ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና መቀበያ ጣቢያዎች ቀደም ብለው የተገነቡ መሆናቸውን ተከትሎ አልፎ አልፎ ለመብራት መቆራረጥና የኃይል መዋዥቅ ምክንያት ናቸው ብለዋል።

ተቋሙ የኃይል መቆራረጥ እንዳይከሰት የቅድመ መከላከልና የጥገና ስራ ከመስራቱ ባሻገር የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችንና ጣቢያዎችን መጪውን ትውልድ ታሳቢ ባደረገ መልኩ የማዘመን ስራ እየተከናወነ መሆኑንም አስረድተዋል፡፡

በሶስት ምዕራፍ ተከፍሎ ስራው የሚከናወን ሲሆን የመጀመሪያው ምዕራፍ አዲስ አበባን ጨምሮ በክልል ዋና ዋና ከተሞች በመሰራት ላይ እንደሚገኝም አመላክተዋል፡፡

ሁለተኛውና ሶስተኛው ምዕራፍ ደግሞ በዕቅዱ መሰረት በሀገሪቱ ትልልቅ ከተሞች የሚቀጥል ይሆናል ነው ያሉት።

በሀገሪቱ 47 ከመቶ የሚሆነው የኃይል መቆራረጥ ችግር ምክንያቱ የኤሌክትሪክ መስመር በተዘረጋባቸው አካባቢዎች በቅርብ ርቀት ባሉ ዛፎች መሆኑን አንስተው ይህንንም የማስተካከል ስራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።

በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ የሚፈጸም ስርቆትም ለኃይል መቆራረጥ ሌላኛው ምክንያት መሆኑን አንስተው የሀገርና የህዝብን ሃብት በጋራ መጠበቅ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026