
አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2017(ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ የ2ኛ ዙር የኮሪደር ልማትሥራዎችን ጎብኝተዋል።
ከንቲባዋ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው በ 2ኛ ዙር የጀመርናቸው ስምንቱን የኮሪደር ልማት ስራዎቻችንን አፈፃፀም ከማለዳ ጀምረን ተዘዋውረን ገምግመናል ሲሉ አስፍረዋል።

አብዛኛዎቹ ስራዎቻችን በተያዘላቸው እቅድ መሰረት በመከናወን ላይ ይገኛሉ ያሉት ከንቲባዋ ስራው በተያዘለት እቅድ መሰረት እንዲጠናቀቅ 24/7 እየሰራችሁ ያላችሁ ሰራተኞች፣ እያስተባበራችሁ ያላችሁ አመራሮች፣ ቦታውን ለልማት በመልቀቅ ወደ ተዘጋጀላችሁ አዲስ ቦታ በፈቃደኝነት በመግባት የተባበራችሁ ውድ ነዋሪዎቻችን የከተማችን ባለውለታዎች ናችሁ ብለዋል።
እንዲሁም ማሽነሪዎቻችሁን ያለ ክፍያ ያበረከታችሁ እንዲሁም አካባቢያችሁን በማፅዳትና ህንፃችሁን በማደስ ከጎናችን የቆማችሁ ውድ የከተማችን ነዋሪዎች ተባብረን ከተማ እየገነባን በመሆኑ ሁላችሁም የከተማችን ባለውለታዎች ናችሁ በማለት በራሳቸውና በከተማ አስተዳደሩ ስም አመስግነዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026