
አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2017(ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ የ2ኛ ዙር የኮሪደር ልማትሥራዎችን ጎብኝተዋል።
ከንቲባዋ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው በ 2ኛ ዙር የጀመርናቸው ስምንቱን የኮሪደር ልማት ስራዎቻችንን አፈፃፀም ከማለዳ ጀምረን ተዘዋውረን ገምግመናል ሲሉ አስፍረዋል።

አብዛኛዎቹ ስራዎቻችን በተያዘላቸው እቅድ መሰረት በመከናወን ላይ ይገኛሉ ያሉት ከንቲባዋ ስራው በተያዘለት እቅድ መሰረት እንዲጠናቀቅ 24/7 እየሰራችሁ ያላችሁ ሰራተኞች፣ እያስተባበራችሁ ያላችሁ አመራሮች፣ ቦታውን ለልማት በመልቀቅ ወደ ተዘጋጀላችሁ አዲስ ቦታ በፈቃደኝነት በመግባት የተባበራችሁ ውድ ነዋሪዎቻችን የከተማችን ባለውለታዎች ናችሁ ብለዋል።
እንዲሁም ማሽነሪዎቻችሁን ያለ ክፍያ ያበረከታችሁ እንዲሁም አካባቢያችሁን በማፅዳትና ህንፃችሁን በማደስ ከጎናችን የቆማችሁ ውድ የከተማችን ነዋሪዎች ተባብረን ከተማ እየገነባን በመሆኑ ሁላችሁም የከተማችን ባለውለታዎች ናችሁ በማለት በራሳቸውና በከተማ አስተዳደሩ ስም አመስግነዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026