የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>ኢትዮ ቴሌኮምና የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የ''ስማርት ኮርት ሲስተም&quot; ን ለመተግበር የሚያስችል የአጋርነት ስምምነት ተፈራረሙ</p>

Jan 15, 2025

IDOPRESS

ባህርዳር፤ ጥር 6/2017(ኢዜአ)፡-ኢትዮ ቴሌኮምና የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የ"ስማርት ኮርት ሲስተም" ን በክልሉ ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል የአጋርነት ስምምነት ተፈራረሙ።

ስምምነቱን የተፈራረሙት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩና የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ አለምአንተ አግደው ናቸው።

''ስማርት ኮርት ሲስተም" የክስ መዝገቦች አያያዝን ማሻሻል፣ በቪዲዮ የተደገፈ የዳኝነት አገልግሎት መስጠት እንዲሁም ተገልጋዮች ባሉበት ሆነው ፋይል እንዲከፍቱ ዕድል የሚፈጥር መሆኑና ሌሎች የዘርፉን አገልግሎት አሰጣጥ የሚያሻሻል ስርዓት መሆኑ ተመልክቷል።


የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ በዚሁ ወቅት እንደገለፁት፤ መንግስታዊ አገልግሎትን ቀልጣፋና ተደራሽ ለማድረግ ዘመኑን የሚመጥን ዲጅታል ቴክኖሎጂን መጠቀም ግድ የሚልበት ደረጃ ላይ ተደርሷል።

''ዛሬ የፍትህ ስርዓትን በቴክኖሎጂ አግዘን ቀልጣፋና ተደራሽ ለማድረግ ከክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ጋር የጋራ ስምምነት በማድረጋችን ደስ ብሎኛል'' ብለዋል።

''የተጣለብንን ኃላፊነት በብቃትና በጥራት ለመወጣት በቁርጠኝነት እንሰራለን'' ሲሉ ተናግረው ኩባኒያው በየተቋማቱ ለዜጎች የሚሰጡ አገልግሎቶችን ለማዘመን አበክሮ እየሰራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ አለምአንተ አግደው በበኩላቸው፤ በክልሉ የፍርድ ቤቶችን አሰራር ለማሻሻል እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።

ፍርድ ቤቶች ስራቸውን በዲጂታል ቴክኖሎጂ ታግዘው ካልሰሩ አገልግሎትን ቀልጣፋና ተደራሽ ማድረግ እንደማይቻል ገልፀው፤ የዳኝነትና የፍትህ ስርዓቱን ቀልጣፋ ለማድረግ ዘመኑ የደረሰበትን ቴክኖሎጂ ተደራሽ ማድረግ ያስፈልጋል ነው ያሉት።

ለዚህም በክልሉ የሚገኙ ፍርድ ቤቶችን በዲጂታል ቴክኖሎጂ በማስተሳሰር የተቀላጠፈ የዳኝነት አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

''የስማርት ኮርት'' አገልግሎት በተለይ ተገልጋዮች ባሉበት ሆነው ፋይል እንዲከፍቱ ትልቅ ዕድልን ይዞ የሚመጣ ከመሆኑም በላይ የተቀላጠፈ የዳኝነት አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ ፋይዳው የጎላ መሆኑን አመልክተዋል።

በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይም የኢትዮ ቴሌኮምና የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የአመራር አባላት ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ባለፉት አምስት ዓመታት አዲስ አበባን የሰላምና የልማት ማዕከል ማድረግ ተችሏል – ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 10/2018(ኢዜአ)፦ ባለፉት አምስት ዓመታት ስር የሰደዱ ችግሮችን በመቅረፍ አዲስ አበባን የሰላምና የልማት ማዕከል ማድረግ መቻሉን የአዲስ...

Jul 18, 2026

በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገበ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገ...

Jun 24, 2026

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026