አዲስ አበባ፤ጥር 6/2017(ኢዜአ)፦የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሰራሮቹን ይበልጥ ለማዘመን ከተለያዩ አጋር አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ መሆኑን የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት ገለጹ።
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የቢዝነስ ልዑክ ጋር ተወያይተዋል።
ዋና ዳይሬክተሯ፥ ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የቢዝነስ ልዑክ ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ምክክር አድርገዋል።
ዋና ዳይሬክተሯ በዚህ ወቅትም ተቋሙ በሪፎርም ሂደት ላይ መሆኑን ገልፀው፥ የሚሰጡ አገልግሎቶች በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ለማደራጀት በርካታ ስራዎች እየተሰሩ እንደሆነና ስራዎችንም ለማዘመን ከተለያዩ አጋር አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
ሁለቱ አካላት ተቋሙ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች ይበልጥ ቀልጣፋ ከማድረግ አኳያ ልዑኩ ያለውን ልምድና ተሞክሮ በሚያጋራበት እንዲሁም በጋራ ሊሰሩ በሚገቡ ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሂደዋል፡፡
የልዑካን ቡድኑ አባላት በበኩላቸው፥ ተቋሙ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም በሚሰጣቸው አገልግሎቶች ላይ በትብብር ለመስራት ፋላጐት እንዳላቸው መግለጻቸውን ከአገልግሎቱ የተገኘ መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025