የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>አገልግሎቱ አሰራሩን ይበልጥ ለማዘመን ከተለያዩ አጋር አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ ነው -ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት</p>

Jan 15, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ጥር 6/2017(ኢዜአ)፦የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሰራሮቹን ይበልጥ ለማዘመን ከተለያዩ አጋር አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ መሆኑን የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት ገለጹ።

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የቢዝነስ ልዑክ ጋር ተወያይተዋል።

ዋና ዳይሬክተሯ፥ ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የቢዝነስ ልዑክ ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ምክክር አድርገዋል።

ዋና ዳይሬክተሯ በዚህ ወቅትም ተቋሙ በሪፎርም ሂደት ላይ መሆኑን ገልፀው፥ የሚሰጡ አገልግሎቶች በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ለማደራጀት በርካታ ስራዎች እየተሰሩ እንደሆነና ስራዎችንም ለማዘመን ከተለያዩ አጋር አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

ሁለቱ አካላት ተቋሙ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች ይበልጥ ቀልጣፋ ከማድረግ አኳያ ልዑኩ ያለውን ልምድና ተሞክሮ በሚያጋራበት እንዲሁም በጋራ ሊሰሩ በሚገቡ ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሂደዋል፡፡

የልዑካን ቡድኑ አባላት በበኩላቸው፥ ተቋሙ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም በሚሰጣቸው አገልግሎቶች ላይ በትብብር ለመስራት ፋላጐት እንዳላቸው መግለጻቸውን ከአገልግሎቱ የተገኘ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026