
አዲስ አበባ፤ጥር 6/2017(ኢዜአ)፦የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሰራሮቹን ይበልጥ ለማዘመን ከተለያዩ አጋር አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ መሆኑን የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት ገለጹ።
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የቢዝነስ ልዑክ ጋር ተወያይተዋል።
ዋና ዳይሬክተሯ፥ ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የቢዝነስ ልዑክ ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ምክክር አድርገዋል።
ዋና ዳይሬክተሯ በዚህ ወቅትም ተቋሙ በሪፎርም ሂደት ላይ መሆኑን ገልፀው፥ የሚሰጡ አገልግሎቶች በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ለማደራጀት በርካታ ስራዎች እየተሰሩ እንደሆነና ስራዎችንም ለማዘመን ከተለያዩ አጋር አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
ሁለቱ አካላት ተቋሙ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች ይበልጥ ቀልጣፋ ከማድረግ አኳያ ልዑኩ ያለውን ልምድና ተሞክሮ በሚያጋራበት እንዲሁም በጋራ ሊሰሩ በሚገቡ ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሂደዋል፡፡
የልዑካን ቡድኑ አባላት በበኩላቸው፥ ተቋሙ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም በሚሰጣቸው አገልግሎቶች ላይ በትብብር ለመስራት ፋላጐት እንዳላቸው መግለጻቸውን ከአገልግሎቱ የተገኘ መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026