አዲስ አበባ፤ጥር 6/2017(ኢዜአ)፦በመዲናዋ የሚከበሩ የአደባባይ በዓላት የቱሪዝም ዘርፍን እና ሀገርን ከማስተዋወቅ ባለፈ የኢኮኖሚ ጠቀሜታቸው ከፍ ያለ መሆኑን የአዲስ አበባ የባህል፣ ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ገለጸ፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የተፈጥሮ ሀብቶችን ፣ታሪካዊ ቅርሶችን እንዲሁም የማይዳሰሱ ትውፊቶችን በአግባቡ ለመጠቀምና በዘርፉ የሚታዩ ችግሮችን ለመፍታት በከፍተኛ ደረጃ እየተሰራ ይገኛል፡፡
ለዚህ ስኬት ደግሞ የአዲስ አበባ ከተማ የቱሪዝም ብራንድና ሎጎ “አፍሪካዊቷ መልኅቅ "በሚል ከሁለት አመት በፊት ተዘጋጅቶ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል፡፡
በአዲስ አበባ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የእንጦጦ ፓርክ፣ አንድነት ፓርክና ወዳጅነት አደባባይን ጨምሮ ማራኪ የቱሪስት መዳረሻዎች እውን ሆነዋል።
የቢሮው ምክትል ሃላፊ ሁንዴ ከበደ እንዳሉት፤ በመዲናዋ የተገነቡት የቱሪስት መዳረሻዎችና በአዲስ እሳቤ እየተተገበረ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ከገጽታ ግንባታ ባለፈ ለኢኮኖሚያዊ እድገት ትልቅ እገዛ አድርገዋል፡፡
በተለይም በመዲናዋ የሚከበሩ የአደባባይ በዓላት የቱሪዝም እድገትን ለማሳለጥ እንዲሁም የከተማዋን ገቢ ከማሳደግ አኳያ ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ ነው፡፡
በመዲናዋ ያሉ የቱሪስት መዳረሻ ቦታዎችን ማስፋት መቻሉ የሀገር ውስጥና የውጭ ጎብኚዎችን ቁጥር በመጨመር ከዘርፉ የሚገኘውን ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ እንዲያድግ ማስቻሉን ተናግረዋል፡፡
በቱሪዝም በመዳረሻዎች አስፈላጊው መሰረት ልማት እንዲሟላ መደረጉ ለጎብኚዎች እርካታ ከመፍጠር ባለፈ ቆይታቸውን እንዲያራዝሙ እያደረገ እንደሚገኝ ነው የገለጹት፡፡
በተለይም በመዲናዋ የተሰሩ የቱሪስት መስህብ ስፍራዎች፣መሰረተ ልማቶች እንዲሁም የኮሪደር ልማት ስራዎች ከፍተኛ የሆነ የኢኮኖሚ ጠቀሜታ እያስገኙ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025