
አዲስ አበባ፤ጥር 6/2017(ኢዜአ)፦በመዲናዋ የሚከበሩ የአደባባይ በዓላት የቱሪዝም ዘርፍን እና ሀገርን ከማስተዋወቅ ባለፈ የኢኮኖሚ ጠቀሜታቸው ከፍ ያለ መሆኑን የአዲስ አበባ የባህል፣ ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ገለጸ፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የተፈጥሮ ሀብቶችን ፣ታሪካዊ ቅርሶችን እንዲሁም የማይዳሰሱ ትውፊቶችን በአግባቡ ለመጠቀምና በዘርፉ የሚታዩ ችግሮችን ለመፍታት በከፍተኛ ደረጃ እየተሰራ ይገኛል፡፡
ለዚህ ስኬት ደግሞ የአዲስ አበባ ከተማ የቱሪዝም ብራንድና ሎጎ “አፍሪካዊቷ መልኅቅ "በሚል ከሁለት አመት በፊት ተዘጋጅቶ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል፡፡
በአዲስ አበባ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የእንጦጦ ፓርክ፣ አንድነት ፓርክና ወዳጅነት አደባባይን ጨምሮ ማራኪ የቱሪስት መዳረሻዎች እውን ሆነዋል።
የቢሮው ምክትል ሃላፊ ሁንዴ ከበደ እንዳሉት፤ በመዲናዋ የተገነቡት የቱሪስት መዳረሻዎችና በአዲስ እሳቤ እየተተገበረ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ከገጽታ ግንባታ ባለፈ ለኢኮኖሚያዊ እድገት ትልቅ እገዛ አድርገዋል፡፡
በተለይም በመዲናዋ የሚከበሩ የአደባባይ በዓላት የቱሪዝም እድገትን ለማሳለጥ እንዲሁም የከተማዋን ገቢ ከማሳደግ አኳያ ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ ነው፡፡
በመዲናዋ ያሉ የቱሪስት መዳረሻ ቦታዎችን ማስፋት መቻሉ የሀገር ውስጥና የውጭ ጎብኚዎችን ቁጥር በመጨመር ከዘርፉ የሚገኘውን ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ እንዲያድግ ማስቻሉን ተናግረዋል፡፡
በቱሪዝም በመዳረሻዎች አስፈላጊው መሰረት ልማት እንዲሟላ መደረጉ ለጎብኚዎች እርካታ ከመፍጠር ባለፈ ቆይታቸውን እንዲያራዝሙ እያደረገ እንደሚገኝ ነው የገለጹት፡፡
በተለይም በመዲናዋ የተሰሩ የቱሪስት መስህብ ስፍራዎች፣መሰረተ ልማቶች እንዲሁም የኮሪደር ልማት ስራዎች ከፍተኛ የሆነ የኢኮኖሚ ጠቀሜታ እያስገኙ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026