የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>በመዲናዋ የሚከበሩ የአደባባይ በዓላት ሀገርን ከማስተዋወቅ ባለፈ የኢኮኖሚ ጠቀሜታቸው ከፍተኛ ነው</p>

Jan 15, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ጥር 6/2017(ኢዜአ)፦በመዲናዋ የሚከበሩ የአደባባይ በዓላት የቱሪዝም ዘርፍን እና ሀገርን ከማስተዋወቅ ባለፈ የኢኮኖሚ ጠቀሜታቸው ከፍ ያለ መሆኑን የአዲስ አበባ የባህል፣ ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ገለጸ፡፡


በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የተፈጥሮ ሀብቶችን ፣ታሪካዊ ቅርሶችን እንዲሁም የማይዳሰሱ ትውፊቶችን በአግባቡ ለመጠቀምና በዘርፉ የሚታዩ ችግሮችን ለመፍታት በከፍተኛ ደረጃ እየተሰራ ይገኛል፡፡


ለዚህ ስኬት ደግሞ የአዲስ አበባ ከተማ የቱሪዝም ብራንድና ሎጎ “አፍሪካዊቷ መልኅቅ "በሚል ከሁለት አመት በፊት ተዘጋጅቶ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል፡፡


በአዲስ አበባ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የእንጦጦ ፓርክ፣ አንድነት ፓርክና ወዳጅነት አደባባይን ጨምሮ ማራኪ የቱሪስት መዳረሻዎች እውን ሆነዋል።


የቢሮው ምክትል ሃላፊ ሁንዴ ከበደ እንዳሉት፤ በመዲናዋ የተገነቡት የቱሪስት መዳረሻዎችና በአዲስ እሳቤ እየተተገበረ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ከገጽታ ግንባታ ባለፈ ለኢኮኖሚያዊ እድገት ትልቅ እገዛ አድርገዋል፡፡


በተለይም በመዲናዋ የሚከበሩ የአደባባይ በዓላት የቱሪዝም እድገትን ለማሳለጥ እንዲሁም የከተማዋን ገቢ ከማሳደግ አኳያ ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ ነው፡፡


በመዲናዋ ያሉ የቱሪስት መዳረሻ ቦታዎችን ማስፋት መቻሉ የሀገር ውስጥና የውጭ ጎብኚዎችን ቁጥር በመጨመር ከዘርፉ የሚገኘውን ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ እንዲያድግ ማስቻሉን ተናግረዋል፡፡


በቱሪዝም በመዳረሻዎች አስፈላጊው መሰረት ልማት እንዲሟላ መደረጉ ለጎብኚዎች እርካታ ከመፍጠር ባለፈ ቆይታቸውን እንዲያራዝሙ እያደረገ እንደሚገኝ ነው የገለጹት፡፡


በተለይም በመዲናዋ የተሰሩ የቱሪስት መስህብ ስፍራዎች፣መሰረተ ልማቶች እንዲሁም የኮሪደር ልማት ስራዎች ከፍተኛ የሆነ የኢኮኖሚ ጠቀሜታ እያስገኙ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026