
ጂንካ፤ ጥር 7/2017(ኢዜአ):- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አሪ ዞን ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ከቦንድ ሽያጭ ከ26 ሚሊዮን ብር በላይ ለማሰባሰብ ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱን የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ።
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የገቢ ማሰባሰብ ንቅናቄ መርሀ ግብር ዛሬ በአሪ ዞን ጂንካ ከተማ ተጀምሯል።
የአሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብረሃም አታ በንቅናቄ መርሀ ግብሩ ላይ እንደገለፁት፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ለማጠናቀቅ በዞኑ ህብረተሰቡን ያሳተፈ የሀብት አሰባሰብ ንቅናቄ ተጀምሯል።
ከጥር 7 ቀን ጀምሮ እስከ ሚያዚያ 2017 ዓ.ም ለአራት ወራት በሚቆየው የቦንድ ሽያጭ ንቅናቄ ከ26 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ለማሰባሰብ ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን ተናግረዋል።

የዞኑ ህዝብም እንደ ወትሮው ቦንድ በመግዛትና ሌሎች ድጋፎችን በማድረግ የሀብት አሰባሰብ ስራው ውጤታማ እንዲሆን እገዛ እንዲያደርግ ጠይቀዋል።
በንቅናቄ መርሀ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡ የጂንካ ከተማ ነዋሪዎች መካከል አቶ ደሳለኝ ደጀኔ እንደገለፁት፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያ የወደፊት ተስፋ በመሆኑ ለግድቡ የሚታጠፍ እጅ የለንም ብለዋል።
የህዳሴ ግድብ የመሰረት ድንጋይ ከተቀመጠበት ጊዜ ጀምሮ ቦንድ በመግዛትና ሌሎች ድጋፎችን ሲያደርጉ መቆየታቸውን ገልጸው፤ አሁንም ቦንድ በመግዛት ተሳትፏቸውን እንደሚያጠናክሩ ገልጸዋል።
የግድቡ ግንባታ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ ለአገልግሎት እስኪበቃ ድጋፋችን አይቋረጥም ያለው ደግሞ ወጣት ባንታየሁ አለሙ ነው።
ለግድቡ ግንባታ ማጠቃለያ የተጀመረውን የሀብት ማሰባሰብ ስራ በስኬት ለማጠናቀቅ ቦንድ በመግዛት እና ህብረተሰቡን በማስተባበር የነቃ ተሳትፎ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል።
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዋንጫ በሚያዚያ ወር ወደ አሪ ዞን እንደሚደርስ የተገለፀ ሲሆን ዋንጫውን በመቀበል የሀብት አሰባሰቡ ላይ በንቃት ለመሳተፍ ዝግጅት መደረጉም ተመልክቷል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026