
አዲስ አበባ፤ ጥር 10/2017(ኢዜአ)፡- መንግሥት ወጣቶችና ሕጻናት በቴክኖሎጂና ዲጂታላይዜሽን ቁልፍ ተዋናይ የሚሆኑበት ምቹ ምህዳር እየፈጠረ መሆኑን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ (ዶ/ር) ገለጹ።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከኢትዮ ሮቦ ሮቦቲክስ የትምህርትና ውድድር ማዕከል ጋር በመተባበር በሰው ሰራሽ አስተውሎት ሲያሰለጥናቸው ለነበሩ ተማሪዎች የዕውቅና ሰጥቷል።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ (ዶ/ር) መንግስት ልዩ ተሰጥኦ ያላቸውን ታዳጊዎች በማሰልጠን ለኢትዮጵያ የቴክኖሎጂና ዲጂታላይዜሽን ጉዞ ዋና ተዋናይ እንዲሆኑ ምቹ ምህዳር እየፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም በርካታ ወጣቶች በተለያዩ ዓለማት በቴክኖሎጂና በፈጠራ ተወዳዳሪ ሆነው ሀገራቸውን ማስጠራት ጀምረዋል ነው ያሉት።
መንግስት የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀው፤ የግሉ ዘርፍም የበኩሉን ሚና እንዲወጣ ጠይቀዋል።
የኢትዮ ሮቦ ሮበቲክስ መስራችና ዋና ስራ አስከያጅ ሰናክሪም መኮንን ስልጠናው ወጣቶች የሳይንስና ቴክኖሎጂ፣ ምህንድስና እና ሂሳብ አተገባበርን በመማር ሮቦትን እንዲቀርጹ የሚያደርግና በሮቦት ኮዲንግና እና ፕሮግራሚንግ ላይ ያተኮረ እንደሆነ ገልጸዋል።

ዕውቅና የተሰጣቸው ተማሪዎች ከዚህ ቀደም በሮቦቲከስ ፕሮግራሚንግና ኢንጅነሪንግ ሰልጥነው በቻይና ሀገር በተካሄደ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ውድድር ላይ በመሳተፍ ሶስተኛ ደረጃን ይዘው በማጠናቀቅ የሜዳሊያና የዋንጫ ተሸላሚ የነበሩ እንደሆኑ ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026