
አዲስ አበባ፤ ጥር 10/2017(ኢዜአ)፡- መንግሥት ወጣቶችና ሕጻናት በቴክኖሎጂና ዲጂታላይዜሽን ቁልፍ ተዋናይ የሚሆኑበት ምቹ ምህዳር እየፈጠረ መሆኑን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ (ዶ/ር) ገለጹ።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከኢትዮ ሮቦ ሮቦቲክስ የትምህርትና ውድድር ማዕከል ጋር በመተባበር በሰው ሰራሽ አስተውሎት ሲያሰለጥናቸው ለነበሩ ተማሪዎች የዕውቅና ሰጥቷል።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ (ዶ/ር) መንግስት ልዩ ተሰጥኦ ያላቸውን ታዳጊዎች በማሰልጠን ለኢትዮጵያ የቴክኖሎጂና ዲጂታላይዜሽን ጉዞ ዋና ተዋናይ እንዲሆኑ ምቹ ምህዳር እየፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም በርካታ ወጣቶች በተለያዩ ዓለማት በቴክኖሎጂና በፈጠራ ተወዳዳሪ ሆነው ሀገራቸውን ማስጠራት ጀምረዋል ነው ያሉት።
መንግስት የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀው፤ የግሉ ዘርፍም የበኩሉን ሚና እንዲወጣ ጠይቀዋል።
የኢትዮ ሮቦ ሮበቲክስ መስራችና ዋና ስራ አስከያጅ ሰናክሪም መኮንን ስልጠናው ወጣቶች የሳይንስና ቴክኖሎጂ፣ ምህንድስና እና ሂሳብ አተገባበርን በመማር ሮቦትን እንዲቀርጹ የሚያደርግና በሮቦት ኮዲንግና እና ፕሮግራሚንግ ላይ ያተኮረ እንደሆነ ገልጸዋል።

ዕውቅና የተሰጣቸው ተማሪዎች ከዚህ ቀደም በሮቦቲከስ ፕሮግራሚንግና ኢንጅነሪንግ ሰልጥነው በቻይና ሀገር በተካሄደ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ውድድር ላይ በመሳተፍ ሶስተኛ ደረጃን ይዘው በማጠናቀቅ የሜዳሊያና የዋንጫ ተሸላሚ የነበሩ እንደሆኑ ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026