የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>ህገ-ወጥ ሞተር ሳይክሎችን ወደ ህጋዊ መስመር ለማስገባት እየተሰራ ነው - የክልል የመንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊዎች</p>

Jan 18, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 9/2017(ኢዜአ)፡- ህገ-ወጥ ሞተር ሳይክሎችን ወደ ህጋዊ መስመር ለማስገባት እየተሰራ መሆኑን የሲዳማና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልሎች የመንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊዎች ገለፁ።

በህገወጥ ሞተር አሽከርካሪዎች የተነሳ የሚደርሰው አደጋ ከቀን ቀን እየጨመረ መምጣቱ ይገለጻል፡፡

አደጋዎቹ በዋናነት መንጃ ፍቃድ በሌላቸውና በህገወጥ ሞተር ተጠቃሚዎች የሚደርስ መሆኑ ደግሞ የጉዳዩን አሳሳቢነት ከፍ ያደርገዋል፡፡

ሰሌዳ አልባ ሞተር ሳይክልና መንጃ ፍቃድ የሌላቸው አሽከርካሪዎችን ወደ ህጋዊነት ለማስገባት በሲዳማና በደቡብ ኢትዮጵያ ክልሎች የተጠናከረ ስራ መጀመሩ ተገልጿል፡፡

ኢዜአ የሲዳማና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልሎች የመንገድ ልማትና ትራንስፖርት ዘርፍ ኃላፊዎችን ህገ-ወጥ የሞተር ሳይክል ተሽከርካሪዎችን ወደ ህጋዊነት ለመመለስ እየሰሩ ባሉት ስራዎች ዙሪያ አነጋግሯል።

የሲዳማ ክልል መንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ ሃላፊ ታምሩ ታፌ እንዳሉት ሞተር ሳይክሎች በክልሉ በገጠር አካባቢዎች የትራንስፖርት አገልግሎት ከመስጠት ባለፈ ለወጣቶች የስራ እድል እየፈጠሩ ነው።

ሞተር ሳይክሎቹን እድሜያቸው ያልደረሰ ለጋ ታዳጊዎች እንደሚያሽከረክሯቸው ገልጸው ጉዳዩን የበለጠ አሳሳቢ ያደረገው ትርፍ በመጫን ከፍጥነት በላይ መጓዛቸው ነው ብለዋል።

በዚህም በክልሉ አብዛኛው የትራፊክ አደጋ በሞተር ሳይክል እንደሚደርስ በመጠቆም ችግሩን ለመፍታት ከትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር ጋር መፍትሄ ለማበጀት እየሰሩ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

በክልሉ ከ40ሺህ በላይ ህገ-ወጥ ሞተር ሳይክሎች መኖራቸውን ገልፀው ለአስተዳደርና በቀላሉ ለመድረስ እንዲመች በማህበር መደራጀታቸውን ተናግረዋል።

የተደራጁት የሞተር ሳይክል አሽከርካሪዎች በመንገድ ደህንነት ዙሪያ ስልጠና እንዲያገኙ መደረጉን ገልፀዋል፡፡

ይህም ባለፉት ስድስት ወራት በሞተር ሳይክል የሚደርስ አደጋ በ49 ነጥብ 5 በመቶ እንዲቀንስ ማስቻሉን ተናግረዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ የትራንስፖርት ዘርፍ ሃላፊ ብርሃኑ ጌቦ(ዶ/ር) በክልሉ ካሉ ሞተሮች ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ህገ-ወጥ መሆናቸውን አስታውቀዋል።

ህገ-ወጥ የሞተር ሳይክሎች ህጋዊ ሂደት እንዲከተሉ ለማድረግ በክልሉ ያሉ ሞተሮችን የመመዝገብ ስራ እየተከናወነ ነው ብለዋል።

ህገ-ወጥ ሞተር ሳይክሎችን ከመመዝገብ ባለፈ ወደ ህጋዊ አሰራር ለማምጣት እየተሰራ መሆኑንም ኃላፊዎቹ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026