የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ተግባራዊ መደረጉ በሐሰተኛ መረጃና ማንነት አገልግሎት ለማግኘት የሚደረግ ሙከራ እንዲቀንስ እያደረገ ነው</p>

Jan 21, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ጥር13/2017(ኢዜአ)፦የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ተግባራዊ መደረጉ ሐሰተኛ መረጃና ማንነት ተጠቅመው ህገ ወጥ አገልግሎት ለማግኘት የሚደረጉ ሙከራዎችን ለመከላከል እያስቻለ መሆኑን የፌዴራል ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት አስታወቀ።


የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሐሚድ ኪኒሶ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ አገልግሎቱ ከፍተኛ መብትና ጥቅምን የሚይዙ ሰነዶችን የማረጋገጥ፣ የማዋዋልና ደኅንነቱን የመጠበቅ አገልግሎት እያከናወነ ይገኛል።


የተቋሙ አሰራር ተገማች፣ ተደራሽ፣ ቀልጣፋ፣ ጥራቱን የጠበቀና ተዓማኒነት ያለው ለማድረግ በቴክኖሎጂ የታገዙ በርካታ የማሻሻያ ስራዎችን ማከናወኑ ውጤታማ እያደረገው ነው።


በዚህም ከተቋሙ የሚወጡ ሰነዶች ተመሳስለው የማይሰሩና በቴክኖሎጂ ለማረጋገጥ የሚያስችሉ መሆናቸውን ገልጸው፤ ባለፉት ስድስት ወራት ለ776 ሺህ ዜጎች አገልግሎት መሰጠቱንም ተናግረዋል።


በዚህም ከተቋማት ጋር የቴክኖሎጂ ትስስር በመፍጠር የማጭበርበር ሙከራዎችን መከላከል መቻሉንም ተናግረዋል፡፡


በተለይም የፋይናንስ ተቋማት፣ከመሬት ልማት፣ ከአሽከርካሪ፤ ተሽከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን፣ ከወሳኝ ኩነት ምዝገባና የዜግነት አገልግሎትና ከሌሎች ተቋማት ጋር በትብብር እየተሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል።


የመኪና ሽያጭ፣ የባንክ ብድር ውል፣ ውክልና፣ የንግድ ማኅበራት መዝገባና ቃለ ጉባኤ መያዝ፣ ቃለ መሃላ፣ ከጋብቻ በፊት ያለ ንብረት ሥምምነትና የተረጋገጡ ዶክመቶችን ለባለመብቶች በሚሰጥበት ወቅት የማረጋገጥ ተግባር መከናወኑን አብራርተዋል።


ከወሳኝ ኩነት ምዝገባና የዜግነት አገልግሎት ጋር በመታወቂያ፣ በጋብቻ ሰርተፍኬት፣ በልደትና መሰል አገልገሎቶች የመረጃ ማጣራትና የመመዝገብ ስራ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል።


በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት ከፓስፖርት፣ መንጃ ፈቃድ፣ የጋብቻ ሰርተፊኬትና ከሌሎች መረጃዎች ጋር በተገናኘ 201 ሐሰተኛ ሰነዶች መያዛቸውን ገልጸዋል፡፡


ለዚህም የፋይዳ ዲጅታል መታወቂያ በአስገዳጅነት ተግባራዊ መደረጉ በሐሰተኛ ሰነድ ለመጠቀም የሚደረጉ ሙከራዎች እንዲቀነሱ አስተዋጽኦ ማድረጉን ተናግረዋል፡፡


በወንጀሉ የተጠረጠሩ ግለሰቦችን ከሚመለከተው አካል ጋር በመቀናጀት በህግ ተጠያቂ እንዲሆኑ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።


እንዲሁም በዲጂታል ማህተም፣የሚታተሙ ሰነዶችን በኤሌክትሮኖክስ ማረጋገጥ የሚያስችል ሚስጥራዊ ህትመት መጀመሩ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የተደገፈ አገልግሎት ከመስጠት ባለፈ ከተለያዩ ተቋማት ጋር ትብብር በመፍጠር እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።


ከክልሎች ጋርም እንዲሁ በመረጃ ቋት ትስስር በመፍጠር በጋራ መሥራት የሚያስችሉ ስረዎች መጀመራቸውን ገልጸዋል።


አገልግሎት ፈላጊ ዜጎች ትክክልኛ ሰነዶችን ብቻ በመያዝ የተፋጠነ አገልግሎት ማግኘነት እንደሚችሉ ገልጸው፥ በሀሰተኛ ሰነድ ለመጠቀም መሞከር በህግ ተጠያቂ እንደሚያደርግም ዋና ዳይሬክተሩ አስገንዝበዋል።


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026