
አዲስ አበባ፤ ጥር 12/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ስድስት ወራት ከ325 ሺህ ሊትር በላይ ነዳጅ በሕገ-ወጥ መንገድ በማጓጓዝ የተሳተፉ ኩባንያዎች 116 ሚሊዮን ብር እንዲቀጡ መደረጉን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገለጹ።
ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት “በጥራት ወደ ተሳለጠ የንግድ ስርዓት” በሚል መሪ ቃል ሚኒስቴሩና የተጠሪ ተቋማት የስድስት ወራት የስራ አፈጻጸም ግምገማ በማካሄድ ላይ እንገኛለን ብለዋል፡፡
ባለፉት ስድስት ወራት በወጪ ንግድ ዘርፍ ወደ 3 ነጥብ 28 ቢሊየን ዶላር ገቢ መገኘቱን ገልጸዋል፡፡
የጥራት መንደር ኢትዮጵያን በሚወክልና በሚያስደንቅ ደረጃ መጠናቀቁ ለሃገር ኩራት ማዕከል ሆኖ የተሳካ ስራ ነው ብለዋል፡፡

በኦንላይን የንግድ ምዝገባና ፍቃድ አሰጣጥ ለንግድ ስርዓት ምቹ እንዲሆን ውጤታማ ስራ መሰራቱን ገልጸው፤ በዚህ ረገድ ብልሹ አሰራሮችን ከማረም አንጻር ህገ ወጥ ተግባር በፈጸሙ 18 የተቋሙ ሰራተኞች ላይ ህጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱንም እንዲሁ።
በበጀት ዓመቱ ባለፉት ስድስት ወራት ከ2 ሚሊዮን 50 ሺህ በላይ የንግድና ምዘገባ ፍቃድ አገልግሎት መሰጠቱን ገልጸው፤ ከባለፈው ዓመት ከተከናወነው 2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ዓመታዊ አፈጻጸም አንፃር ሲታይ በጣም ከፍተኛ አፈፃፀም መሆኑን አንስተዋል፡፡
ነዳጅ ግብይትን ስርዓት ለማስያዝ በተሰራ ስራ በህገ-ወጥ መንገድ ሲጓጓዝ የነበረ 325 ሺ ሊትር ነዳጅ በቁጥጥር ስር መዋሉንና ኩባንያዎች 116 ሚሊዮን ብር እንዲቀጡ መደረጉን ተናግረዋል።
በሲሚንቶ ግብይት ማሻሻያ የተረጋጋ አቅርቦትና ግብይት እንዲኖር በመደረጉ ዋጋው በግማሽ መቀኑን ጠቅሰዋል።
በጨው ግብይት ሪፎርምም በጥቂት ናጋዴዎች በሞኖፖልሊ ተይዞ የነበረውን ግብይት በፍትሃዊነት ለሁሉም ክፍት መደረጉንም እነዲሁ።
የዓለም የንግድ ድርጅት አባልነት ተቋርጦ ከነበረበት ምዕራፍ በማውጣት ወደ ንቁ ድርድር ዐውድ መግባቱን ጠቅሰው፤ ለቀጣይ 5ኛ ዙር ድርድርም ብቃት ያላቸውን ሙያተኞችን በማደራጀት በቂ ዝግጅት እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026