
አዲስ አበባ፤ ጥር 13/2017(ኢዜአ)፦በ2016/17 የመኸር ምርት ዘመን ከተሰበሰበው ሰብል እስካሁን 420 ሚሊየን ኩንታል ምርት መገኘቱን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።
የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ መለስ መኮንን (ዶ/ር) በምርት ዘመኑ 20 ነጥብ 5 ሚሊየን ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብሎች መሸፈኑን አንስተው፤ ከዚህም 614 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለማግኘት ታቅዷል ብለዋል።
ከአጠቃላዩ እስካሁን 18 ነጥብ 3 ሚሊየን ሄክታር ላይ የደረሰ ሰብል መሰብሰቡን ገልጸው፥ ተሰብስቦ ከተወቃው ሰብል ደግሞ 420 ሚሊየን ኩንታል ምርት መገኘቱን ገልጸዋል።

የምርት አሰባሰብ ስራው ብክነትን በሚቀንስ መልኩ በተቀናጀ ሁኔታ በቴክኖሎጂ ታግዞ እየተካሄደ መሆኑን ሚኒስትር ዴኤታው ጠቅሰዋል።
በቀጣይም ዘግይተው የተዘሩ ሰብሎች የምርት ስብሰባም እንደሚከናወን አመላክተዋል።
በሌላ በኩል በሀገሪቱ የእርሻ ስራን ከዘር መዝራት እስከ ምርት መሰብሰብ የሚያዘምኑ ተግባራት እየጨመሩ መሆናቸውን ሚኒስትር ዴኤታው አብራርተዋል።
ዘመናዊ የእርሻ መሳሪያዎችን የአስተራረስ ስልቶች እየተተገበሩ መሆኑን ጠቅሰው፥ ለአብነትም የኩታ ገጠም እርሻ በየዓመቱ እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል።
ለአብነትም ባለፈው የመኸር ዓመት 8 ነጥብ 6 ሚሊየን ሄክታር መሬት በኩታ ገጠም ዘዴ መታረሱን ጠቅሰው በ2016/17 ምርት ዘመን ወደ 12 ነጥብ 4 ሚሊየን ሄክታር መሬት ማደጉን ነው ያብራሩት።
ይህም የምርት ጥራትንና ምርታማነትን የሚያሳድግ ነው ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026