የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>በምርት ዘመኑ ከተሰበሰበው የመኸር ሰብል እስካሁን 420 ሚሊየን ኩንታል ምርት ተገኝቷል- የግብርና ሚኒስቴር</p>

Jan 22, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 13/2017(ኢዜአ)፦በ2016/17 የመኸር ምርት ዘመን ከተሰበሰበው ሰብል እስካሁን 420 ሚሊየን ኩንታል ምርት መገኘቱን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።

የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ መለስ መኮንን (ዶ/ር) በምርት ዘመኑ 20 ነጥብ 5 ሚሊየን ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብሎች መሸፈኑን አንስተው፤ ከዚህም 614 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለማግኘት ታቅዷል ብለዋል።

ከአጠቃላዩ እስካሁን 18 ነጥብ 3 ሚሊየን ሄክታር ላይ የደረሰ ሰብል መሰብሰቡን ገልጸው፥ ተሰብስቦ ከተወቃው ሰብል ደግሞ 420 ሚሊየን ኩንታል ምርት መገኘቱን ገልጸዋል።


የምርት አሰባሰብ ስራው ብክነትን በሚቀንስ መልኩ በተቀናጀ ሁኔታ በቴክኖሎጂ ታግዞ እየተካሄደ መሆኑን ሚኒስትር ዴኤታው ጠቅሰዋል።

በቀጣይም ዘግይተው የተዘሩ ሰብሎች የምርት ስብሰባም እንደሚከናወን አመላክተዋል።

በሌላ በኩል በሀገሪቱ የእርሻ ስራን ከዘር መዝራት እስከ ምርት መሰብሰብ የሚያዘምኑ ተግባራት እየጨመሩ መሆናቸውን ሚኒስትር ዴኤታው አብራርተዋል።

ዘመናዊ የእርሻ መሳሪያዎችን የአስተራረስ ስልቶች እየተተገበሩ መሆኑን ጠቅሰው፥ ለአብነትም የኩታ ገጠም እርሻ በየዓመቱ እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል።

ለአብነትም ባለፈው የመኸር ዓመት 8 ነጥብ 6 ሚሊየን ሄክታር መሬት በኩታ ገጠም ዘዴ መታረሱን ጠቅሰው በ2016/17 ምርት ዘመን ወደ 12 ነጥብ 4 ሚሊየን ሄክታር መሬት ማደጉን ነው ያብራሩት።

ይህም የምርት ጥራትንና ምርታማነትን የሚያሳድግ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026