
አዲስ አበባ፤ ጥር 13/2017(ኢዜአ)፦በ2016/17 የመኸር ምርት ዘመን ከተሰበሰበው ሰብል እስካሁን 420 ሚሊየን ኩንታል ምርት መገኘቱን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።
የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ መለስ መኮንን (ዶ/ር) በምርት ዘመኑ 20 ነጥብ 5 ሚሊየን ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብሎች መሸፈኑን አንስተው፤ ከዚህም 614 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለማግኘት ታቅዷል ብለዋል።
ከአጠቃላዩ እስካሁን 18 ነጥብ 3 ሚሊየን ሄክታር ላይ የደረሰ ሰብል መሰብሰቡን ገልጸው፥ ተሰብስቦ ከተወቃው ሰብል ደግሞ 420 ሚሊየን ኩንታል ምርት መገኘቱን ገልጸዋል።

የምርት አሰባሰብ ስራው ብክነትን በሚቀንስ መልኩ በተቀናጀ ሁኔታ በቴክኖሎጂ ታግዞ እየተካሄደ መሆኑን ሚኒስትር ዴኤታው ጠቅሰዋል።
በቀጣይም ዘግይተው የተዘሩ ሰብሎች የምርት ስብሰባም እንደሚከናወን አመላክተዋል።
በሌላ በኩል በሀገሪቱ የእርሻ ስራን ከዘር መዝራት እስከ ምርት መሰብሰብ የሚያዘምኑ ተግባራት እየጨመሩ መሆናቸውን ሚኒስትር ዴኤታው አብራርተዋል።
ዘመናዊ የእርሻ መሳሪያዎችን የአስተራረስ ስልቶች እየተተገበሩ መሆኑን ጠቅሰው፥ ለአብነትም የኩታ ገጠም እርሻ በየዓመቱ እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል።
ለአብነትም ባለፈው የመኸር ዓመት 8 ነጥብ 6 ሚሊየን ሄክታር መሬት በኩታ ገጠም ዘዴ መታረሱን ጠቅሰው በ2016/17 ምርት ዘመን ወደ 12 ነጥብ 4 ሚሊየን ሄክታር መሬት ማደጉን ነው ያብራሩት።
ይህም የምርት ጥራትንና ምርታማነትን የሚያሳድግ ነው ብለዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026