የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

<p>በክልሉ ከ12 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት 158 የመስኖ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ ነው</p>

Jan 22, 2025

IDOPRESS

ደሴ፤ ጥር 13/2017(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ከ12 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት ተመድቦ 158 የተለያዩ የመስኖ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ መስኖና ቆላማ አካባቢዎች ልማት ቢሮ አስታወቀ።

በደቡብ ወሎ ዞን ደሴ ዙሪያ ወረዳ ከ62 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባ የመስኖ ፕሮጀክት ዛሬ ተመርቋል።

የክልሉ መስኖና ቆላማ አካባቢዎች ልማት ቢሮ ኃላፊ ዳኝነት ፈንታ (ዶ/ር) እንደገለጹት የክልሉ መንግስት የከርስና የገጸ ምድር ውሃን በማልማት አርሶ አደሩን በመስኖ ተጠቃሚ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ ነው።

በዚህም አሁን ላይ በክልሉ ከ12 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት ተመድቦ የ158 የተለያዩ የመስኖ ፕሮጀክቶች በግንባታ ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል።

በተያዘው ዓመት 22 የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ መጠናቀቃቸውን ገልጸው፤ የ95ቱ ግንባታ ደግሞ በጀት ዓመቱ መጨረሻ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው ብለዋል።

የመስኖ ፕሮጀክቶቹ ተጠናቀው ወደ ስራ ሲገቡ ከ26 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በአዲስ መልክ በማልማት የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ እንደሆኑ ገልጸዋል።

በሌላ በኩል በክልሉ ከ80 ሺህ ሄክታር መሬት በላይ ማልማት የሚችሉ 110 የመስኖ ፕሮጀክቶች ዲዛይንና ጥናት እየተካሄደ መሆኑንም ገልጸዋል።

የደቡብ ወሎ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አሊ ይማም በበኩላቸው የዞኑን ሰላም ከማስጠበቅ ጎን ለጎን ታላላቅ የኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፋይዳ ያላቸው ፕሮጀክቶች ግንባታ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በዘንድሮ ዓመት ብቻ በከፍተኛ ወጪ የተሰሩ 18 የተለያዩ የመስኖ ፕሮጀክቶች ተመርቀው አገልግሎት መጀመራቸውን ጠቅሰዋል።

በደቡብ ወሎ ዞን ብቻ ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚገነቡ የመስኖ ፕሮጀክቶች እንዳሉ አስረድተዋል።

የደሴ ዙሪያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጀማል መሀመድ በበኩላቸው በወረዳው የጅርቲ ወንዝ ላይ 62 ሚሊዮን ብር የተገነባው የመስኖ ፕሮጀክት ዛሬ ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።

ፕሮጀክቱ 200 ሄክታር የሚጠጋ መሬት በማልማት ከ700 በላይ አርሶ አደሮች በዓመት ሶስት ጊዜ በማምረት ተጠቃሚ ያደርጋል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025