የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>በክልሉ ከ12 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት 158 የመስኖ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ ነው</p>

Jan 22, 2025

IDOPRESS

ደሴ፤ ጥር 13/2017(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ከ12 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት ተመድቦ 158 የተለያዩ የመስኖ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ መስኖና ቆላማ አካባቢዎች ልማት ቢሮ አስታወቀ።

በደቡብ ወሎ ዞን ደሴ ዙሪያ ወረዳ ከ62 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባ የመስኖ ፕሮጀክት ዛሬ ተመርቋል።

የክልሉ መስኖና ቆላማ አካባቢዎች ልማት ቢሮ ኃላፊ ዳኝነት ፈንታ (ዶ/ር) እንደገለጹት የክልሉ መንግስት የከርስና የገጸ ምድር ውሃን በማልማት አርሶ አደሩን በመስኖ ተጠቃሚ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ ነው።

በዚህም አሁን ላይ በክልሉ ከ12 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት ተመድቦ የ158 የተለያዩ የመስኖ ፕሮጀክቶች በግንባታ ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል።

በተያዘው ዓመት 22 የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ መጠናቀቃቸውን ገልጸው፤ የ95ቱ ግንባታ ደግሞ በጀት ዓመቱ መጨረሻ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው ብለዋል።

የመስኖ ፕሮጀክቶቹ ተጠናቀው ወደ ስራ ሲገቡ ከ26 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በአዲስ መልክ በማልማት የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ እንደሆኑ ገልጸዋል።

በሌላ በኩል በክልሉ ከ80 ሺህ ሄክታር መሬት በላይ ማልማት የሚችሉ 110 የመስኖ ፕሮጀክቶች ዲዛይንና ጥናት እየተካሄደ መሆኑንም ገልጸዋል።

የደቡብ ወሎ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አሊ ይማም በበኩላቸው የዞኑን ሰላም ከማስጠበቅ ጎን ለጎን ታላላቅ የኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፋይዳ ያላቸው ፕሮጀክቶች ግንባታ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በዘንድሮ ዓመት ብቻ በከፍተኛ ወጪ የተሰሩ 18 የተለያዩ የመስኖ ፕሮጀክቶች ተመርቀው አገልግሎት መጀመራቸውን ጠቅሰዋል።

በደቡብ ወሎ ዞን ብቻ ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚገነቡ የመስኖ ፕሮጀክቶች እንዳሉ አስረድተዋል።

የደሴ ዙሪያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጀማል መሀመድ በበኩላቸው በወረዳው የጅርቲ ወንዝ ላይ 62 ሚሊዮን ብር የተገነባው የመስኖ ፕሮጀክት ዛሬ ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።

ፕሮጀክቱ 200 ሄክታር የሚጠጋ መሬት በማልማት ከ700 በላይ አርሶ አደሮች በዓመት ሶስት ጊዜ በማምረት ተጠቃሚ ያደርጋል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026