
ደሴ፤ ጥር 13/2017(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ከ12 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት ተመድቦ 158 የተለያዩ የመስኖ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ መስኖና ቆላማ አካባቢዎች ልማት ቢሮ አስታወቀ።
በደቡብ ወሎ ዞን ደሴ ዙሪያ ወረዳ ከ62 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባ የመስኖ ፕሮጀክት ዛሬ ተመርቋል።
የክልሉ መስኖና ቆላማ አካባቢዎች ልማት ቢሮ ኃላፊ ዳኝነት ፈንታ (ዶ/ር) እንደገለጹት የክልሉ መንግስት የከርስና የገጸ ምድር ውሃን በማልማት አርሶ አደሩን በመስኖ ተጠቃሚ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ ነው።
በዚህም አሁን ላይ በክልሉ ከ12 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት ተመድቦ የ158 የተለያዩ የመስኖ ፕሮጀክቶች በግንባታ ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል።
በተያዘው ዓመት 22 የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ መጠናቀቃቸውን ገልጸው፤ የ95ቱ ግንባታ ደግሞ በጀት ዓመቱ መጨረሻ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው ብለዋል።
የመስኖ ፕሮጀክቶቹ ተጠናቀው ወደ ስራ ሲገቡ ከ26 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በአዲስ መልክ በማልማት የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ እንደሆኑ ገልጸዋል።
በሌላ በኩል በክልሉ ከ80 ሺህ ሄክታር መሬት በላይ ማልማት የሚችሉ 110 የመስኖ ፕሮጀክቶች ዲዛይንና ጥናት እየተካሄደ መሆኑንም ገልጸዋል።
የደቡብ ወሎ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አሊ ይማም በበኩላቸው የዞኑን ሰላም ከማስጠበቅ ጎን ለጎን ታላላቅ የኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፋይዳ ያላቸው ፕሮጀክቶች ግንባታ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በዘንድሮ ዓመት ብቻ በከፍተኛ ወጪ የተሰሩ 18 የተለያዩ የመስኖ ፕሮጀክቶች ተመርቀው አገልግሎት መጀመራቸውን ጠቅሰዋል።
በደቡብ ወሎ ዞን ብቻ ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚገነቡ የመስኖ ፕሮጀክቶች እንዳሉ አስረድተዋል።
የደሴ ዙሪያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጀማል መሀመድ በበኩላቸው በወረዳው የጅርቲ ወንዝ ላይ 62 ሚሊዮን ብር የተገነባው የመስኖ ፕሮጀክት ዛሬ ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።
ፕሮጀክቱ 200 ሄክታር የሚጠጋ መሬት በማልማት ከ700 በላይ አርሶ አደሮች በዓመት ሶስት ጊዜ በማምረት ተጠቃሚ ያደርጋል ብለዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026