አዲስ አበባ፤ጥር 22/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት የለውጥ አመታት ለመጪው ቴክኖሎጂ ዝግጁ የሚያደርጉ ምቹ መደላድሎች መፈጠራቸውን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አስታወቀ።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ይሹሩን አለማየሁ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት ከለውጡ በኋላ ባሉት አመታት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ተዘጋጅቶ ወደ ትግበራ በመገባቱ በዘርፉ በርካታ ለውጦች መጥተዋል።
እስካሁን ባለው 11 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዜጎች ለዲጂታል መታወቂያ መመዝገባቸውን ገልፀው፥ የዲጂታል ክፍያ አማራጮችን የማስፋት ስራ እየተሰራ መሆኑንም አስረድተዋል።
በዚህም የቴሌኮምና ኤሌክትሮኒክስ ተደራሽነትን በማስፋት በኩል ውጤታማ ስራ መከናወኑን ጠቅሰው፥ ኔትወርኩን ከ 2 ጂ ወደ 5 ጂ ማሳደግ መቻሉን ተናግረዋል።
ከ800 በላይ የመንግስት አገልግሎቶች በኦንላይን እየተሰጡ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
አስተማማኝ የዲጂታል ስርዓት ለመፍጠር በተከናወኑ ተግባራት ጠንካራ የሳይበር ደህንነት ተቋም መገንባቱን አብራርተዋል።
በአምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያዊያን ኮደርስ መርኃ ግብር ከ460 ሺህ በላይ ዜጎች ለስልጠና መመዝገባቸውንና ከእነዚህም ውስጥ ከ127 ሺህ በላይ የምስክር ወረቀት መውሰዳቸውን ገልፀዋል።
በለውጡ አመታት ስታርት አፖችን ለማበረታታት የሚያስችሉና ለመጪው ቴክኖሎጂ ዝግጁ የሚያደርጉ ምቹ መደላድሎች መፈጠራቸውንና የተለያዩ የህግ ማዕቀፎች መዘጋጀታቸውንም አስረድተዋል።
የለውጡ ሂደት የሚኒስቴሩን አቅም በማሳደግ ቴክኖሎጂን ከመቅዳት በራስ ወደ መፍጠር ያሸጋገረና ለገበያ የሚቀርቡ የፈጠራ ውጤቶች እንዲበራከቱ ማድረጉንም ጠቁመዋል።
ጥራቱን የጠበቀ ምርት ለአለም አቀፍ ገበያ ለማቅረብ የሚያስችል የጥራት መንደር መገንባቱንም ገልፀዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025