
አዲስ አበባ፤ጥር 22/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት የለውጥ አመታት ለመጪው ቴክኖሎጂ ዝግጁ የሚያደርጉ ምቹ መደላድሎች መፈጠራቸውን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አስታወቀ።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ይሹሩን አለማየሁ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት ከለውጡ በኋላ ባሉት አመታት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ተዘጋጅቶ ወደ ትግበራ በመገባቱ በዘርፉ በርካታ ለውጦች መጥተዋል።
እስካሁን ባለው 11 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዜጎች ለዲጂታል መታወቂያ መመዝገባቸውን ገልፀው፥ የዲጂታል ክፍያ አማራጮችን የማስፋት ስራ እየተሰራ መሆኑንም አስረድተዋል።
በዚህም የቴሌኮምና ኤሌክትሮኒክስ ተደራሽነትን በማስፋት በኩል ውጤታማ ስራ መከናወኑን ጠቅሰው፥ ኔትወርኩን ከ 2 ጂ ወደ 5 ጂ ማሳደግ መቻሉን ተናግረዋል።
ከ800 በላይ የመንግስት አገልግሎቶች በኦንላይን እየተሰጡ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
አስተማማኝ የዲጂታል ስርዓት ለመፍጠር በተከናወኑ ተግባራት ጠንካራ የሳይበር ደህንነት ተቋም መገንባቱን አብራርተዋል።
በአምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያዊያን ኮደርስ መርኃ ግብር ከ460 ሺህ በላይ ዜጎች ለስልጠና መመዝገባቸውንና ከእነዚህም ውስጥ ከ127 ሺህ በላይ የምስክር ወረቀት መውሰዳቸውን ገልፀዋል።
በለውጡ አመታት ስታርት አፖችን ለማበረታታት የሚያስችሉና ለመጪው ቴክኖሎጂ ዝግጁ የሚያደርጉ ምቹ መደላድሎች መፈጠራቸውንና የተለያዩ የህግ ማዕቀፎች መዘጋጀታቸውንም አስረድተዋል።
የለውጡ ሂደት የሚኒስቴሩን አቅም በማሳደግ ቴክኖሎጂን ከመቅዳት በራስ ወደ መፍጠር ያሸጋገረና ለገበያ የሚቀርቡ የፈጠራ ውጤቶች እንዲበራከቱ ማድረጉንም ጠቁመዋል።
ጥራቱን የጠበቀ ምርት ለአለም አቀፍ ገበያ ለማቅረብ የሚያስችል የጥራት መንደር መገንባቱንም ገልፀዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026