የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>በሀረሪ ክልል የኮሪደር ልማቱን በምሽትም ጭምር በማከናወን ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ ነው-አቶ ኦርዲን በድሪ</p>

Feb 7, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 29/2017(ኢዜአ)፦በሃረሪ ክልል የኮሪደር ልማት ስራዎችን በምሽት ጭምር በማከናወን ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ገለፁ።

ርዕሰ መስተዳድሩ በሀረር ከተማ የኮሪደር ልማት የምሽት ስራ እንቅስቃሴዎችን የመንገድ ዳር መብራቶች፤ የአባዲር ፕላዛና የአረንጓዴ ልማት ስራዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።


የኮሪደር ልማት ስራውን በጥራትና በፍጥነት አጠናቆ ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ ትኩረት መሰጠቱን የገለፁት ርዕሰ መስተዳድሩ በተለይ ስራዎችን በምሽት ጭምር የማከናወን የስራ ባህልን በማዳበር ተጨባጭ ለውጥ እያሳየ መሆኑን ተናግረዋል።

የኮሪደር ልማቱ ከተማዋን ለኑሮ ምቹ በማድረግ የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት ታሳቢ ባደረገ መልኩ እየተሰራ እንደሚገኝም አክለዋል።

በተለይ የሀረር ከተማን ገፅታ ከመቀየር ባለፈ ለበርካታ ወገኖች የስራ እድል በመፍጠር በኢኮኖሚ ተጠቃሚ እያደረገ እንደሚገኝ መግለጻቸውን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኮሪደር ልማቱ ለነዋሪውና ለቱሪስቶች የተመቸች ዘመናዊ ከተማን ለመፍጠር የሚያግዝ መሆኑን በመጠቆም ስራዎችን በፍጥነት ለማጠናቀቅ የምሽት ፈረቃ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ገልጸዋል።

በመስክ ምልከታው ላይ የክልሉ ካቢኔ አባላት ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026