
አዲስ አበባ፤ ጥር 29/2017(ኢዜአ)፦በሃረሪ ክልል የኮሪደር ልማት ስራዎችን በምሽት ጭምር በማከናወን ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ገለፁ።
ርዕሰ መስተዳድሩ በሀረር ከተማ የኮሪደር ልማት የምሽት ስራ እንቅስቃሴዎችን የመንገድ ዳር መብራቶች፤ የአባዲር ፕላዛና የአረንጓዴ ልማት ስራዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።

የኮሪደር ልማት ስራውን በጥራትና በፍጥነት አጠናቆ ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ ትኩረት መሰጠቱን የገለፁት ርዕሰ መስተዳድሩ በተለይ ስራዎችን በምሽት ጭምር የማከናወን የስራ ባህልን በማዳበር ተጨባጭ ለውጥ እያሳየ መሆኑን ተናግረዋል።
የኮሪደር ልማቱ ከተማዋን ለኑሮ ምቹ በማድረግ የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት ታሳቢ ባደረገ መልኩ እየተሰራ እንደሚገኝም አክለዋል።
በተለይ የሀረር ከተማን ገፅታ ከመቀየር ባለፈ ለበርካታ ወገኖች የስራ እድል በመፍጠር በኢኮኖሚ ተጠቃሚ እያደረገ እንደሚገኝ መግለጻቸውን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
የኮሪደር ልማቱ ለነዋሪውና ለቱሪስቶች የተመቸች ዘመናዊ ከተማን ለመፍጠር የሚያግዝ መሆኑን በመጠቆም ስራዎችን በፍጥነት ለማጠናቀቅ የምሽት ፈረቃ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ገልጸዋል።
በመስክ ምልከታው ላይ የክልሉ ካቢኔ አባላት ተገኝተዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026