የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>ለምርት ዘመኑ 13 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ግዥ ተፈጽሟል - ግብርና ሚኒስቴር</p>

Feb 8, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦ ለ2017/18 የምርት ዘመን 13 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ግዥ መፈፀሙን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።

የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ሶፊያ ካሳ(ዶ/ር) ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ መንግስት ለግብርናው ዘርፍ ልዩ ትኩረት መስጠቱን ተከትሎ በዘርፉ አመርቂ ውጤት እየተመዘገበ ነው።

መንግስት ዘርፉን ለማሳደግ በትኩረት ከሚሰራባቸው ጉዳዮች አንዱ የአፈር ማዳበሪያ ግዥ መሆኑን አስታውቀዋል።

በዚህም ለ2017/18 የምርት ዘመን የሚውል የአፈር ማዳበሪያ ከጂቡቲ ወደብ ወደ ኢትዮጵያ የማጓጓዝ ስራ በከፍተኛ ትጋት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡

በምርት ዘመኑ 24 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ግዥ ለመፈፀም ታቅዶ 13 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኩንታል ግዥ መፈፀሙን ተናግረዋል።

የአፈር ማዳበሪያውም አምና ከነበረው አቅርቦት የአራት ሚሊዮን ኩንታል ብልጫ እንዳለውም ሚኒስትር ዴኤታዋ ገልፀዋል።

ከተገዛው 13 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኩንታል ውስጥ 6 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኩንታል የሚሆነው ጂቡቲ ወደብ መድረሱን በመጥቀስ አሁን ላይ ከ4 ሚሊዬዮን ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ወደ ሀገር ውስጥ መግባቱን ተናግረዋል።

የአፈር ማዳበሪያውን ከማጓጓዝ ጎን ለጎን የአርሶ አደሩን አቅም ባገናዘበ መልኩ የማስራጨት ስራ ይከናወናል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025