
መተማ፤ የካቲት 1/2017 (ኢዜአ)፡-መተማ ሁለገብ የገበሬዎች ሕብረት ሥራ ማህበራት ዩኒየን አርሶ አደሮችንና ሸማቹን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ለማድረግ የጀመራቸውን ሥራዎች አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ።
ዩኒየኑ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን ዛሬ በገንዳውሃ ከተማ አካሄዷል።

የዩኒዬኑ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሀብቴ ዘውዱ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ ዩኒየኑ በዞኑ ሦስት ወረዳዎችና ሁለት ከተማ አስተዳደሮች 47 ማህበራትንና 29 ሺህ የሚጠጉ አርሶ አደሮችን አቅፎ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።
በዚህም ለአርሶ አደሮች ምርጥ ዘር፣ የአፈር ማዳበሪያ፣ ፀረ አረም፣ የእንስሳት መድኃኒት እና መሰረታዊ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን የማህበረሰብ ክፍሎች የኑሮ ጫና ለማቃለል ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የፍጆታ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ገበያውን እያረጋጋ መሆኑንም ተናግረዋል።
የግብርና ምርቶችን እሴት ጨምሮ ለውጭ ገበያ ለማቅረብ ዩኒየኑ ትኩረት ስጥቶ ሲሰራ መቆየቱንም አስታውሰዋል።
ለእዚህም በዓመት ከ40 ሺህ ኩንታል በላይ ሰሊጥ ማበጠር የሚችል የሰሊጥ ማበጠሪያ ማሽን ማዘጋጀቱን ገልጸዋል።
በቀጣይም የጥጥ መዳመጫና የዘይት ፋብሪካ ለማቋቋም ዕቅድ መያዙን ጠቅሰው፣ አርሶ አደሮችንና ሸማቹን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ለማድረግ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል።
የምዕራብ ጎንደር ዞን ሕብረት ሥራ ማህበራት ማስፋፊያ ተጠሪ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ በልጣ ጌትነት በበኩላቸው እንዳሉት፣ ዩኒየኑ ካለው የሰው ሀይልና ሀብት የተነሳ አገልግሎቱን ይበልጥ ማጠናከር ይኖርበታል።
ዩኒየኑ ባለው የሰሊጥ ማበጠሪያ ማሽን ሰሊጥን እሴት ጨምሮ ለውጭ ገበያ ለማቅረብ የሚደረገውን ጥረት እየደገፈ መሆኑንም ተናግረዋል።
ዩኒየኑ ካፒታል በማሳደግ የአባላቱንና የህብረተሰቡን ችግር ለመፍታት እየሰጣቸው ያሉ አገልግሎቶችን ማሳደግ እንዳለበትም አስገንዝበዋል።
አርሶ አደር አምባው ገብረእግዚአብሔር በመተማ ወረዳ የኮኪት ቀበሌ ነዋሪ ሲሆኑ ዩኒየኑ የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ ግብአትን ከማቅረብ ጀምሮ ለእንስሶቻቸው የጤና አገልግሎት እየሰጣቸው መሆኑን ገልፀዋል።
በዚህም አርሶ አደሩ ተጠቃሚ እየሆነ መጥቷል ያሉት አርሶ አደሩ፣ የግብርና ግብአቶችን ተጠቅመው ማልማት ከጀመሩ ወዲህ ተጠቃሚነታቸው እያደገ መሆኑንን ገልጸዋል።
የገንዳውኃ ከተማ ሸማቾች ሕብረት ሥራ ማህበር አመራር አቶ ሙሉዓለም ጌታሁን በበኩላቸው፣ ዩኒየኑ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶችን ከሌላ አካባቢ በማምጣት ለሸማቹ በማድረስ ገበያ የማረጋጋት ሥራ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
መተማ የገበሬዎች ሁለገብ የሕብረት ሥራ ማህበራት ዩኒየን በ1992 ዓ.ም በ52 ሺህ ብር ካፒታል የተመሰረተ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ጠቅላላ ሀብቱ ከ75 ሚሊዮን ብር በላይ መድረሱም ታውቋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026