የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>ዩኒየኑ አርሶ አደሮችንና ሸማቹን ተጠቃሚ ለማድረግ የጀመራቸውን ሥራዎች እንደሚያጠናክር አስታወቀ</p>

Feb 10, 2025

IDOPRESS

መተማ፤ የካቲት 1/2017 (ኢዜአ)፡-መተማ ሁለገብ የገበሬዎች ሕብረት ሥራ ማህበራት ዩኒየን አርሶ አደሮችንና ሸማቹን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ለማድረግ የጀመራቸውን ሥራዎች አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ።

ዩኒየኑ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን ዛሬ በገንዳውሃ ከተማ አካሄዷል።


የዩኒዬኑ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሀብቴ ዘውዱ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ ዩኒየኑ በዞኑ ሦስት ወረዳዎችና ሁለት ከተማ አስተዳደሮች 47 ማህበራትንና 29 ሺህ የሚጠጉ አርሶ አደሮችን አቅፎ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።

በዚህም ለአርሶ አደሮች ምርጥ ዘር፣ የአፈር ማዳበሪያ፣ ፀረ አረም፣ የእንስሳት መድኃኒት እና መሰረታዊ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን የማህበረሰብ ክፍሎች የኑሮ ጫና ለማቃለል ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የፍጆታ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ገበያውን እያረጋጋ መሆኑንም ተናግረዋል።

የግብርና ምርቶችን እሴት ጨምሮ ለውጭ ገበያ ለማቅረብ ዩኒየኑ ትኩረት ስጥቶ ሲሰራ መቆየቱንም አስታውሰዋል።

ለእዚህም በዓመት ከ40 ሺህ ኩንታል በላይ ሰሊጥ ማበጠር የሚችል የሰሊጥ ማበጠሪያ ማሽን ማዘጋጀቱን ገልጸዋል።

በቀጣይም የጥጥ መዳመጫና የዘይት ፋብሪካ ለማቋቋም ዕቅድ መያዙን ጠቅሰው፣ አርሶ አደሮችንና ሸማቹን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ለማድረግ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል።

የምዕራብ ጎንደር ዞን ሕብረት ሥራ ማህበራት ማስፋፊያ ተጠሪ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ በልጣ ጌትነት በበኩላቸው እንዳሉት፣ ዩኒየኑ ካለው የሰው ሀይልና ሀብት የተነሳ አገልግሎቱን ይበልጥ ማጠናከር ይኖርበታል።

ዩኒየኑ ባለው የሰሊጥ ማበጠሪያ ማሽን ሰሊጥን እሴት ጨምሮ ለውጭ ገበያ ለማቅረብ የሚደረገውን ጥረት እየደገፈ መሆኑንም ተናግረዋል።

ዩኒየኑ ካፒታል በማሳደግ የአባላቱንና የህብረተሰቡን ችግር ለመፍታት እየሰጣቸው ያሉ አገልግሎቶችን ማሳደግ እንዳለበትም አስገንዝበዋል።

አርሶ አደር አምባው ገብረእግዚአብሔር በመተማ ወረዳ የኮኪት ቀበሌ ነዋሪ ሲሆኑ ዩኒየኑ የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ ግብአትን ከማቅረብ ጀምሮ ለእንስሶቻቸው የጤና አገልግሎት እየሰጣቸው መሆኑን ገልፀዋል።

በዚህም አርሶ አደሩ ተጠቃሚ እየሆነ መጥቷል ያሉት አርሶ አደሩ፣ የግብርና ግብአቶችን ተጠቅመው ማልማት ከጀመሩ ወዲህ ተጠቃሚነታቸው እያደገ መሆኑንን ገልጸዋል።

የገንዳውኃ ከተማ ሸማቾች ሕብረት ሥራ ማህበር አመራር አቶ ሙሉዓለም ጌታሁን በበኩላቸው፣ ዩኒየኑ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶችን ከሌላ አካባቢ በማምጣት ለሸማቹ በማድረስ ገበያ የማረጋጋት ሥራ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

መተማ የገበሬዎች ሁለገብ የሕብረት ሥራ ማህበራት ዩኒየን በ1992 ዓ.ም በ52 ሺህ ብር ካፒታል የተመሰረተ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ጠቅላላ ሀብቱ ከ75 ሚሊዮን ብር በላይ መድረሱም ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026