የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>በቴክኖሎጂ የተደገፈ የአሰራር ሥርዓት በመዘርጋት ክህሎት መር የሰብል ምርታማነትን ባህል የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው - ግብርና ሚኒስቴር</p>

Feb 10, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፦ በቴክኖሎጂ የተደገፈ የአሰራር ሥርዓት በመዘርጋት ክህሎት መር የሰብል ምርታማነትን ባህል የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር ገለጸ።

በአዳማ ከተማ ለፌዴራልና ክልሎች የስራ ኃላፊዎችና ሙያተኞች በሰብል አመራረት ፓኬጅ፣ ግብርና ኤክስቴንሽን፣ የአፈር ለምነትና የኩታ ገጠም አስተራረስ ዘዴ የአሰልጣኞች ስልጠና ተሰጥቷል።


የግብርና ሚኒስትር ዴዔታ መለስ መኮንን(ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የሰብል ምርታማነት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ፣ የወጪ ንግድን በመጠንና በጥራት ማምረት፣ ገቢ የኢንዱስትሪ ግብዓትን መተካትና የስራ ዕድል ፈጠራን ማሳደግ ያስቻሉ ስኬቶች ተመዝግበዋል።


የግብርና ዕድገትን ለማሳለጥ ከፌዴራል እስከ ቀበሌ ለአርሶ አደሮች ስልጠናዎችን በመስጠት የተሰናሰለ እና ዘመናዊ የምርታማነት ሥርዓት ለመዘርጋት እንደሚሰራ አስረድተዋል።


በዚህም የግብርና ምርታማነት ስኬቶችን በማስቀጠል በቴክኖሎጂ የተደገፈ የአሰራር ሥርዓት በመዘርጋት ክህሎት መር የሰብል ምርታማነትን ባህል ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል።


የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ በሪሶ ፈይሳ፤ ሀገራዊ ለውጡ የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ እመርታዊ ዕድገት ማስመዝገብ ያስቻሉ የማሻሻያ እርምጃዎች የተወሰዱበት መሆኑን ገልጸዋል።


በዚሁ መነሻነትም በክልሉ በሁሉም የግብርና ምርታማነት መስክ ከዝግጅት እስከ ምርት ስብሰባ ድረስ ስኬታማ እርምጃዎችን በመውሰድ አርሶ አደሩ ተጠቃሚ እንዲሆን እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል።


የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ ቃልኪዳን ሽፈራው፤ የክልሉን የሰብል ልማት አቅም ታሳቢ በማድረግ በኩታ ገጠምና ሜካናይዜሽን እርሻ ልማት ስኬታማ ስራ መሰራቱን ገልጸዋል።


በምርት ዘመኑም ለምግብነት፣ ለኢንዱስትሪ ግብዓት እና ወጪ ንግድ ጉልህ ፋይዳ ያላቸው ሰብሎችን በማልማት በምግብ እራስን የመቻል ሀገራዊ ግብ ማሳካት ያስቻሉ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል።


የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የእርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ እያሱ አብርሃ(ዶ/ር)፤ በሁሉም የግብርና ልማት መስክ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ማሳደግ ያስቻሉ ስራዎች መሰራታቸውን አብራርተዋል።


የፌዴራል መንግስትና ባለድርሻ አካላት የአፈር ማዳበሪያና ምርጥ ዘር ግብዓት አቅርቦት ላይ ያደረጉት ድጋፍ የሰብል ምርታማነት፣ ጥራትና ተወዳዳሪነት በማሳደግ ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልጸዋል።


የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ ዓለም-ይርጋ ወልደ-ሥላሴ፤ በክልሉ የግብርና ምርታማነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እመርታዊ ውጤት እያስመዘገበ እንደሚገኝ ገልጸዋል።


"የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሰብል ምርታማነትን ማሳደግ" በሚል መሪ ሃሳብ የተሰጠው የአሰልጣኞች ስልጠናም የእርሻና ሆርቲካልቸር ምርታማነትን የሚያሳድጉ አሰራሮችን በመዘርጋት ዘመናዊ የሰብል፣ የመስኖ፣ የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት፣ የእፅዋት ጥበቃና ኤክስቴንሽን አገልግሎትን ስራዎችን ለማስፋፋት ጉለህ አበርክቶ እንደሚኖረው ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026