የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>በቴክኖሎጂ የተደገፈ የአሰራር ሥርዓት በመዘርጋት ክህሎት መር የሰብል ምርታማነትን ባህል የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው - ግብርና ሚኒስቴር</p>

Feb 10, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፦ በቴክኖሎጂ የተደገፈ የአሰራር ሥርዓት በመዘርጋት ክህሎት መር የሰብል ምርታማነትን ባህል የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር ገለጸ።

በአዳማ ከተማ ለፌዴራልና ክልሎች የስራ ኃላፊዎችና ሙያተኞች በሰብል አመራረት ፓኬጅ፣ ግብርና ኤክስቴንሽን፣ የአፈር ለምነትና የኩታ ገጠም አስተራረስ ዘዴ የአሰልጣኞች ስልጠና ተሰጥቷል።


የግብርና ሚኒስትር ዴዔታ መለስ መኮንን(ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የሰብል ምርታማነት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ፣ የወጪ ንግድን በመጠንና በጥራት ማምረት፣ ገቢ የኢንዱስትሪ ግብዓትን መተካትና የስራ ዕድል ፈጠራን ማሳደግ ያስቻሉ ስኬቶች ተመዝግበዋል።


የግብርና ዕድገትን ለማሳለጥ ከፌዴራል እስከ ቀበሌ ለአርሶ አደሮች ስልጠናዎችን በመስጠት የተሰናሰለ እና ዘመናዊ የምርታማነት ሥርዓት ለመዘርጋት እንደሚሰራ አስረድተዋል።


በዚህም የግብርና ምርታማነት ስኬቶችን በማስቀጠል በቴክኖሎጂ የተደገፈ የአሰራር ሥርዓት በመዘርጋት ክህሎት መር የሰብል ምርታማነትን ባህል ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል።


የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ በሪሶ ፈይሳ፤ ሀገራዊ ለውጡ የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ እመርታዊ ዕድገት ማስመዝገብ ያስቻሉ የማሻሻያ እርምጃዎች የተወሰዱበት መሆኑን ገልጸዋል።


በዚሁ መነሻነትም በክልሉ በሁሉም የግብርና ምርታማነት መስክ ከዝግጅት እስከ ምርት ስብሰባ ድረስ ስኬታማ እርምጃዎችን በመውሰድ አርሶ አደሩ ተጠቃሚ እንዲሆን እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል።


የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ ቃልኪዳን ሽፈራው፤ የክልሉን የሰብል ልማት አቅም ታሳቢ በማድረግ በኩታ ገጠምና ሜካናይዜሽን እርሻ ልማት ስኬታማ ስራ መሰራቱን ገልጸዋል።


በምርት ዘመኑም ለምግብነት፣ ለኢንዱስትሪ ግብዓት እና ወጪ ንግድ ጉልህ ፋይዳ ያላቸው ሰብሎችን በማልማት በምግብ እራስን የመቻል ሀገራዊ ግብ ማሳካት ያስቻሉ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል።


የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የእርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ እያሱ አብርሃ(ዶ/ር)፤ በሁሉም የግብርና ልማት መስክ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ማሳደግ ያስቻሉ ስራዎች መሰራታቸውን አብራርተዋል።


የፌዴራል መንግስትና ባለድርሻ አካላት የአፈር ማዳበሪያና ምርጥ ዘር ግብዓት አቅርቦት ላይ ያደረጉት ድጋፍ የሰብል ምርታማነት፣ ጥራትና ተወዳዳሪነት በማሳደግ ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልጸዋል።


የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ ዓለም-ይርጋ ወልደ-ሥላሴ፤ በክልሉ የግብርና ምርታማነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እመርታዊ ውጤት እያስመዘገበ እንደሚገኝ ገልጸዋል።


"የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሰብል ምርታማነትን ማሳደግ" በሚል መሪ ሃሳብ የተሰጠው የአሰልጣኞች ስልጠናም የእርሻና ሆርቲካልቸር ምርታማነትን የሚያሳድጉ አሰራሮችን በመዘርጋት ዘመናዊ የሰብል፣ የመስኖ፣ የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት፣ የእፅዋት ጥበቃና ኤክስቴንሽን አገልግሎትን ስራዎችን ለማስፋፋት ጉለህ አበርክቶ እንደሚኖረው ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026