የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የትራንስፖርት ዘርፍ ተዋናዮችን የሚያገናኝ የዲጂታል መተግበሪያ አስጀመረ</p>

Feb 11, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 3/2017(ኢዜአ)፦በትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የለማ የትራንስፖርት ኦፕሬተሮችንና የጭነት ባለቤቶችን የሚገናኝ የዲጂታል መተግበሪያ አስጀምሯል።

በማሪታይም ባለስልጣን ስትራቴጂና ፖሊሲዎች ውስጥ ከተጠቅሱ የመፍትሄ ሃሳቦች ውስጥ በትራንስፖርት ዘርፍ የሚስተዋሉ የድለላና የቅንጅት ጉድለቶችን መስመር በማስያዝ ተዋናዮችን የሚያገናኝ መተግበሪያ በማፍለቅ ጥቅም ላይ እንዲውል መደረጉ ተገልጿል።

በዚህም የትራንስፖርትና ሎጂስቲከስ ሚኒስቴር፣ የባለስልጣኑ፣ የግሉ ዘርፍ እንዲሁም በመንግስት-የግል አጋርነት የሚፈጸሙ 40 የሚደርሱ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ፕሮጀክቶችን ጥቅም ላይ ማዋሉ ተገልጿል።

ፕሮጀክቶቹ በዘርፉ የመሰረተ ልማት ግንባታን፣ የአገልግሎት ማቀላጠፈያ ሥርዓትን፣ የጭነት እና የህዝብ ትራንስፖርት የአገልግሎት አቅም ግንባታ መርሃ ግብሮች የሚሳለጡበት እንደሆኑ ተነስቷል።

በዚህም መተግበሪያው በመንግስት ክትትል የግሉን ዘርፍ በማሳተፍ ያለውን የመረጃ ግንኙነት እና አገልግሎት የማሳልጥ የቴክኖሎጂ የአሰራር ሥርዓት መሆኑ ተመላክቷል።

መተግበሪያው በዩናይትድ አፍሪካ ሎጂስቲክስ የቴከኖሎጂ ኩባንያ እና ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በሰራው ስኬታማ ተግባር የተቀናጀ የቴክኖሎጂ ሥርዓት "Digital Freight Marketplace systems" የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል።

በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር አብዱልበር ሸምሱ፣ የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ዴንጌ ቦሩ እና ሌሎች የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ተዋናዮች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025