የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የትራንስፖርት ዘርፍ ተዋናዮችን የሚያገናኝ የዲጂታል መተግበሪያ አስጀመረ</p>

Feb 11, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 3/2017(ኢዜአ)፦በትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የለማ የትራንስፖርት ኦፕሬተሮችንና የጭነት ባለቤቶችን የሚገናኝ የዲጂታል መተግበሪያ አስጀምሯል።

በማሪታይም ባለስልጣን ስትራቴጂና ፖሊሲዎች ውስጥ ከተጠቅሱ የመፍትሄ ሃሳቦች ውስጥ በትራንስፖርት ዘርፍ የሚስተዋሉ የድለላና የቅንጅት ጉድለቶችን መስመር በማስያዝ ተዋናዮችን የሚያገናኝ መተግበሪያ በማፍለቅ ጥቅም ላይ እንዲውል መደረጉ ተገልጿል።

በዚህም የትራንስፖርትና ሎጂስቲከስ ሚኒስቴር፣ የባለስልጣኑ፣ የግሉ ዘርፍ እንዲሁም በመንግስት-የግል አጋርነት የሚፈጸሙ 40 የሚደርሱ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ፕሮጀክቶችን ጥቅም ላይ ማዋሉ ተገልጿል።

ፕሮጀክቶቹ በዘርፉ የመሰረተ ልማት ግንባታን፣ የአገልግሎት ማቀላጠፈያ ሥርዓትን፣ የጭነት እና የህዝብ ትራንስፖርት የአገልግሎት አቅም ግንባታ መርሃ ግብሮች የሚሳለጡበት እንደሆኑ ተነስቷል።

በዚህም መተግበሪያው በመንግስት ክትትል የግሉን ዘርፍ በማሳተፍ ያለውን የመረጃ ግንኙነት እና አገልግሎት የማሳልጥ የቴክኖሎጂ የአሰራር ሥርዓት መሆኑ ተመላክቷል።

መተግበሪያው በዩናይትድ አፍሪካ ሎጂስቲክስ የቴከኖሎጂ ኩባንያ እና ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በሰራው ስኬታማ ተግባር የተቀናጀ የቴክኖሎጂ ሥርዓት "Digital Freight Marketplace systems" የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል።

በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር አብዱልበር ሸምሱ፣ የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ዴንጌ ቦሩ እና ሌሎች የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ተዋናዮች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026