የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>የመንግሥት አገልግሎት አስተዳደር ፖሊሲ ማስፈጸሚያ ስትራቴጂዎችና የአሰራር መመሪያዎች ዝግጅት ተጠናቋል - ኮሚሽነር መኩሪያ ኃይሌ(ዶ/ር)</p>

Feb 11, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 3/2017(ኢዜአ)፡- የመንግሥት አገልግሎት አስተዳደር ፖሊሲ ማስፈጸሚያ ስትራቴጂዎችና የአሰራር መመሪያዎች ዝግጅት መጠናቀቁን የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽነር መኩሪያ ኃይሌ(ዶ/ር) አስታወቁ።

የተሟላ የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርምን እውን ለማድረግ አስፈላጊ ዝግጅቶች እየተደረጉ መሆኑንም ገልጸዋል።

ኮሚሽነር መኩሪያ ኃይሌ(ዶ/ር) እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ ጊዜው የሚጠይቀውን ዘመናዊ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ ሁሉን አቀፍ የለውጥ ሥራዎች ተግባራዊ እየተደረጉ ናቸው።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ለውጡን ተከትሎ በሰጡት አቅጣጫ መሰረት በሲቪል ሰርቪስ አገልግሎት ዘርፍ በሰው ኃይል፣ በቴክኖሎጂ እና አደረጃጀት ላይ መሰረታዊ ለውጥ የሚያመጡ ዝግጅቶች እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።

ለዚህም ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር የአሰራር ሥርዓት እየተዘረጋ መሆኑን ገልጸው፤ የዓለም እና አህጉር አቀፍ እንዲሁም ሀገር አቀፍ ተሞክሮዎች ተዳሰው የተካተቱበት የመንግሥት አገልግሎት አስተዳደር ፖሊሲ መዘጋጀቱን ተናግረዋል።

ፖሊሲው በሚኒስትሮች ምክር ቤት መጽደቁን ጠቅሰው፤ ፖሊሲውን ለማስፈጸም የሚረዱ ስትራቴጂዎች፣ የአሰራር መመሪያዎች ዝግጅት መጠናቀቁን ገልጸዋል።

እንደ ኮሚሽነር መኩሪያ ገለጻ፤ የማስፈጸሚያ አዋጅ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጸደቀ ሲሆን፤ ስታንዳርድ ዝግጅትም በስፋት እየተሰራበት ነው።

በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያላቸው 70 ስታንዳርዶችን ተግባራዊ ለማድረግም እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።

በፌዴራልና በክልሎች የሚሰሩ ሥራዎች እንዴት መናበብ ይችላሉ? አደረጃጀቱ እንዴት ውጤታማ በሆነ መልኩ ይከናወናል በሚለው ዙሪያ ጥልቅ የሆነ የለውጥ ሥራዎች በሂደት ላይ ናቸው ብለዋል።

ሰራተኞች በሥራ አፈጻጸማቸው ተመዝነው የማትጊያ ማበረታቻዎች የሚያገኙበት ሥርዓት እንደሚዘረጋ ጠቁመው፤ ይህም ለሥራ ውጤታማነት መሻሻል አወንታዊ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው አስረድተዋል።

ሲቪል ሰርቪስ አገልግሎቱን ወደ አዲስ ምዕራፍ ለማሸጋገር የኢትዮጵያን ነባራዊ ሁኔታ ታሳቢ ያደረገ የመፍትሄ እርምጃዎችን መውሰድ ከለውጥ ሥራዎች መካከል የሚጠቀስ መሆኑን ተናግረዋል።

የለውጥ ሥራዎቹ ግባቸውን እንዲያሳኩ ሁሉም ዜጋ የድርሻውን መወጣት እንዳለበት ጠቁመው፤ አገልግሎቱን የማሻሻል ሥራው ለመንግሥት ብቻ የሚተው አይደለም ብለዋል።

የመንግሥት ሰራተኛው ከጊዜው ጋር ራሱን እያዘመነ እንዲሁም የመፈጸም አቅሙን እያሻሻለ መሄድ እንደሚጠበቅበትም ነው ኮሚሽነር መኩሪያ ሀይሌ(ዶ/ር) ያመላከቱት።

ተገልጋዮችም የሚገጥማቸውን የመልካም አስተዳደር ችግሮች ለሚመለከታቸው አካላት ጥቆማ በመስጠትና በማጋለጥ የመፍትሄው አካል መሆን እንደሚገባቸው አጽንኦት ሰጥተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026