
ባህርዳር፤ የካቲት 3/2017(ኢዜአ)፡- የብልጽግና ፓርቲ በ2ኛው ጉባኤ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት የተሳለጠና ዘመናዊ የሲቪል ሰርቪስ አገልግሎት ለመስጠት በትኩረት እንደሚሰራ የአማራ ክልል ሲቪል ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ኮሚሽን አስታወቀ።
ኮሚሽኑ በብልጽግና ፓርቲ የመጀመሪያ ጉባኤ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት በተከናወኑ ተግባራትና በ2ኛው ጉባኤ አቅጣጫዎች ላይ ማምሻውን የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ወይዘሮ ባንቻምላክ ገብረ ማሪያም መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም በመጀመሪያው ጉባኤ የሲቪል ሰርቪስ ተቋማት ነጻና ገለልተኛ በሆነ መንገድ አገልግሎት እንዲሰጡ አቅጣጫ ተቀምጦ እንደነበር አስታውሰዋል።
በዚህም የተቋማትን አገልግሎት አሰጣጥ ችግር፣ መንስኤና የመፍትሄ አቅጣጫ የሚያመላክት ጥናት እስከ ወረዳ ድረስ መከናወኑን ገልጸዋል።
የመጀመሪያው የፓርቲው ጉባኤ የትግበራ ጊዜ ሲቪል ሰርቪሱን ለማዘመን እንደ ዝግጅት ምዕራፍ መወሰዱን ጠቁመው በቀጣይ የጥናቱን ግኝት መሰረት በማድረግ ወደ ተግባር ይገባል ብለዋል።
ለዚህም የብልጽግና ፓርቲ በ2ኛው ጉባኤ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት የተሳለጠና ዘመናዊ የሲቪል ሰርቪስ አገልግሎት ለመስጠት በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አስታውቀዋል።
በተለይም በየተቋማቱ ያለውን ሰራተኛ የአቅም ክፍተት መሙላት የሚያስችል ስራ እንደሚከናወን ጠቁመው ከዚህ ጎን ለጎንም ተጠያቂነትን ለማስፈን ይሰራል ነው ያሉት።
በክልሉ ያለውን የሲቪል ሰርቪስ አገልግሎት ዘመናዊ፣ ቀልጣፋና ፍትሃዊ በማድረግ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ማቃለል በሚያስችል መልኩ እንደሚፈጸምም በመግለጫቸው አመላክተዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026