የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>በአማራ ክልል የተሳለጠና ዘመናዊ የሲቪል ሰርቪስ አገልግሎት ለመስጠት በትኩረት ይሰራል - ኮሚሽኑ</p>

Feb 11, 2025

IDOPRESS

ባህርዳር፤ የካቲት 3/2017(ኢዜአ)፡- የብልጽግና ፓርቲ በ2ኛው ጉባኤ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት የተሳለጠና ዘመናዊ የሲቪል ሰርቪስ አገልግሎት ለመስጠት በትኩረት እንደሚሰራ የአማራ ክልል ሲቪል ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ኮሚሽን አስታወቀ።

ኮሚሽኑ በብልጽግና ፓርቲ የመጀመሪያ ጉባኤ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት በተከናወኑ ተግባራትና በ2ኛው ጉባኤ አቅጣጫዎች ላይ ማምሻውን የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ወይዘሮ ባንቻምላክ ገብረ ማሪያም መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫቸውም በመጀመሪያው ጉባኤ የሲቪል ሰርቪስ ተቋማት ነጻና ገለልተኛ በሆነ መንገድ አገልግሎት እንዲሰጡ አቅጣጫ ተቀምጦ እንደነበር አስታውሰዋል።

በዚህም የተቋማትን አገልግሎት አሰጣጥ ችግር፣ መንስኤና የመፍትሄ አቅጣጫ የሚያመላክት ጥናት እስከ ወረዳ ድረስ መከናወኑን ገልጸዋል።

የመጀመሪያው የፓርቲው ጉባኤ የትግበራ ጊዜ ሲቪል ሰርቪሱን ለማዘመን እንደ ዝግጅት ምዕራፍ መወሰዱን ጠቁመው በቀጣይ የጥናቱን ግኝት መሰረት በማድረግ ወደ ተግባር ይገባል ብለዋል።

ለዚህም የብልጽግና ፓርቲ በ2ኛው ጉባኤ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት የተሳለጠና ዘመናዊ የሲቪል ሰርቪስ አገልግሎት ለመስጠት በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አስታውቀዋል።

በተለይም በየተቋማቱ ያለውን ሰራተኛ የአቅም ክፍተት መሙላት የሚያስችል ስራ እንደሚከናወን ጠቁመው ከዚህ ጎን ለጎንም ተጠያቂነትን ለማስፈን ይሰራል ነው ያሉት።

በክልሉ ያለውን የሲቪል ሰርቪስ አገልግሎት ዘመናዊ፣ ቀልጣፋና ፍትሃዊ በማድረግ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ማቃለል በሚያስችል መልኩ እንደሚፈጸምም በመግለጫቸው አመላክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026