
ባህርዳር፤ የካቲት 3/2017(ኢዜአ)፡- የብልጽግና ፓርቲ በ2ኛው ጉባኤ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት የተሳለጠና ዘመናዊ የሲቪል ሰርቪስ አገልግሎት ለመስጠት በትኩረት እንደሚሰራ የአማራ ክልል ሲቪል ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ኮሚሽን አስታወቀ።
ኮሚሽኑ በብልጽግና ፓርቲ የመጀመሪያ ጉባኤ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት በተከናወኑ ተግባራትና በ2ኛው ጉባኤ አቅጣጫዎች ላይ ማምሻውን የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ወይዘሮ ባንቻምላክ ገብረ ማሪያም መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም በመጀመሪያው ጉባኤ የሲቪል ሰርቪስ ተቋማት ነጻና ገለልተኛ በሆነ መንገድ አገልግሎት እንዲሰጡ አቅጣጫ ተቀምጦ እንደነበር አስታውሰዋል።
በዚህም የተቋማትን አገልግሎት አሰጣጥ ችግር፣ መንስኤና የመፍትሄ አቅጣጫ የሚያመላክት ጥናት እስከ ወረዳ ድረስ መከናወኑን ገልጸዋል።
የመጀመሪያው የፓርቲው ጉባኤ የትግበራ ጊዜ ሲቪል ሰርቪሱን ለማዘመን እንደ ዝግጅት ምዕራፍ መወሰዱን ጠቁመው በቀጣይ የጥናቱን ግኝት መሰረት በማድረግ ወደ ተግባር ይገባል ብለዋል።
ለዚህም የብልጽግና ፓርቲ በ2ኛው ጉባኤ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት የተሳለጠና ዘመናዊ የሲቪል ሰርቪስ አገልግሎት ለመስጠት በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አስታውቀዋል።
በተለይም በየተቋማቱ ያለውን ሰራተኛ የአቅም ክፍተት መሙላት የሚያስችል ስራ እንደሚከናወን ጠቁመው ከዚህ ጎን ለጎንም ተጠያቂነትን ለማስፈን ይሰራል ነው ያሉት።
በክልሉ ያለውን የሲቪል ሰርቪስ አገልግሎት ዘመናዊ፣ ቀልጣፋና ፍትሃዊ በማድረግ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ማቃለል በሚያስችል መልኩ እንደሚፈጸምም በመግለጫቸው አመላክተዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026