ታርጫ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፦ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ከአዝርትና ሆርቲካልቸር ሰብሎች ከ40 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለጹ።
ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በታርጫ ከተማ እየተካሄደ ባለው የምክር ቤት ጉባኤ የአስፈፃሚ ተቋማት የግማሽ ዓመት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርትን ሲያቀርቡ እንደገለጹት፣ ምርቱ የተሰበሰበው በመኸር እርሻ ከለማው ነው።
በእርሻና በእንስሳት ዘርፍ የሚፈለገውን ውጤት ለማግኘት በቅንጅት በተሰራ ሥራም አበረታች ውጤት መገኘቱን ተናግረዋል።
ባለፉት ስድስት ወራት በመኸር አዝመራ ከለማው 384 ሺህ 786 ሄክታር መሬት ከ17 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡን ገልጸዋል።
ከዚህ ውስጥ 90 ሺህ 297 ሄክታሩ በክላስተር የለማ መሆኑን አስታውሰው፣ ይህም አምራቾች ከክላስተር ልማት የተሻለ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ልምድ ያገኙበት መሆኑን ተናግረዋል።
ከ159 ሺህ ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ ሆርቲካልቸር፣ አትክልትና ሥራሥር እንዲሁም እንሰት በማልማት 23 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡን ነው ያስረዱት።
የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ በግማሽ በጀት ዓመቱ 146 ሺህ ኩንታል የሚጠጋ የአፈር ማዳበሪያ ተሰራጭቷል ብለዋል።
ከ31 ሺህ በላይ እንስሳትን በማዳቀል አርሶና አርብቶ አደሮችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ገልፀው፤ ከ12 ሺህ ሄክታር በሚበልጥ ማሳ ላይ የመኖ ልማት ሥራ ተከናውኗል ብለዋል።
ባለፈ የተሻለ ምርት የሚሰጥ የቡና ዝርያ ችግኝ ዝግጅት ሥራ ትኩረት መሰጠቱን ገልጸው፤ በ13 ሺህ 535 ሄክታር ማሳ ላይ አዳዲስ የቅመማ ቅመም ልማት ችግኝ ተከላ ሥራ መከናወኑን አስታውቀዋል።
ባለፉት ስድስት ወራት የማር ምርታማነትን ለማሳደግ በተደረገው ጥረት ከ57 ሺህ በላይ ዘመናዊ፣ የሽግግርና ጨፈቃ ቀፎች መሰራጨታቸውን ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025