
ታርጫ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፦ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ከአዝርትና ሆርቲካልቸር ሰብሎች ከ40 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለጹ።
ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በታርጫ ከተማ እየተካሄደ ባለው የምክር ቤት ጉባኤ የአስፈፃሚ ተቋማት የግማሽ ዓመት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርትን ሲያቀርቡ እንደገለጹት፣ ምርቱ የተሰበሰበው በመኸር እርሻ ከለማው ነው።
በእርሻና በእንስሳት ዘርፍ የሚፈለገውን ውጤት ለማግኘት በቅንጅት በተሰራ ሥራም አበረታች ውጤት መገኘቱን ተናግረዋል።
ባለፉት ስድስት ወራት በመኸር አዝመራ ከለማው 384 ሺህ 786 ሄክታር መሬት ከ17 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡን ገልጸዋል።
ከዚህ ውስጥ 90 ሺህ 297 ሄክታሩ በክላስተር የለማ መሆኑን አስታውሰው፣ ይህም አምራቾች ከክላስተር ልማት የተሻለ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ልምድ ያገኙበት መሆኑን ተናግረዋል።
ከ159 ሺህ ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ ሆርቲካልቸር፣ አትክልትና ሥራሥር እንዲሁም እንሰት በማልማት 23 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡን ነው ያስረዱት።
የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ በግማሽ በጀት ዓመቱ 146 ሺህ ኩንታል የሚጠጋ የአፈር ማዳበሪያ ተሰራጭቷል ብለዋል።
ከ31 ሺህ በላይ እንስሳትን በማዳቀል አርሶና አርብቶ አደሮችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ገልፀው፤ ከ12 ሺህ ሄክታር በሚበልጥ ማሳ ላይ የመኖ ልማት ሥራ ተከናውኗል ብለዋል።
ባለፈ የተሻለ ምርት የሚሰጥ የቡና ዝርያ ችግኝ ዝግጅት ሥራ ትኩረት መሰጠቱን ገልጸው፤ በ13 ሺህ 535 ሄክታር ማሳ ላይ አዳዲስ የቅመማ ቅመም ልማት ችግኝ ተከላ ሥራ መከናወኑን አስታውቀዋል።
ባለፉት ስድስት ወራት የማር ምርታማነትን ለማሳደግ በተደረገው ጥረት ከ57 ሺህ በላይ ዘመናዊ፣ የሽግግርና ጨፈቃ ቀፎች መሰራጨታቸውን ተናግረዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026