
አዲስ አበባ፤ የካቲት 5/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት አፍሪካ በምግብ ራሷን እንደምትችል ማረጋገጫ ነው ሲሉ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ገለጹ።
ዓለም አቀፍ የመስኖ ልማትና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ምርታማነት ጉባኤ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።

በጉባኤው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ የአየር ንብረት ለውጥና የምግብ ዋስትና ችግር እየተባባሰ መሆኑን ገልጸዋል።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አመራር ኢትዮጵያ በአፍሪካ ማህብረሰብ አቀፍ የግብርና ልማት ሽግግርን እየመራች ነው ብለዋል።
የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋምን ታሳቢ ያደረጉ የምግብ ምርታማነት ሥራዎችን እያከናወነች መሆኗን ጠቅሰው፥ ለአብነትም የአረንጓዴ አሻራ መርሐግብርን ጠቅሰዋል።
በዚህ መርሐግብር 40 ቢሊዮን ችግኝ መትከላችን ብቻ የደን ሽፋንን ከማሳደጉም በላይ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች የምግብ ዋስትናቸውን እያረጋገጡ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ሌላኛው የአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የግብርና ኢኒሼቲቭ የስንዴ ልማት መሆኑን ጠቅሰው፥ በዚህም የሚገባ ስንዴን በማቆም የስንዴ ምርት ፍጆታዋን በራሷ አቅም ማምረት ችላለች ብለዋል።
ይህም አፍሪካ ራሷን መመገብ እንደምትችል ማረጋገጫ ነው ያሉት ፕሬዚዳንቱ፥ ለመስኖ፣ ለሜካናይዜሽንና ሌሎች የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋሙ የግብርና ስርዓቶች ትኩረት በመስጠት የምግብ ሉዓላዊነቷን ታረጋግጣለች ብለዋል።
ኢትዮጵያ የሌማት ትሩፋትን በመጀመር በቤተሰብ ደረጃ የተመጣጠነ የምግብ ስርዓትን የሚያረጋግጡ የወተት፣ የእንቁላል፣ የማርና ሌሎችንም ምርቶች ላይ በማተኮር ውጤታማ ስራዎችን እየሰራች መሆኑንም ጠቅሰዋል።
አፍሪካም ሌማቷን መሙላት የሚያስችላት አቅም አላት ያሉት ፕሬዚዳንቱ የኢትዮጵያ ተሞክሮ ለአህጉሪቱ የሚተርፍ እንደሆነም አንስተዋል።
በመስኖ ልማትም በርካታ የግብርና ስራዎች እየተከናወኑ ነው ያሉት ፕሬዚዳንቱ አርብቶ አደሮችን ጭምር ወደዚህ መርሐግብር ማሳተፍ ተችሏል ነው ያሉት።
የመስኖ ፕሮጀክቶቻችን የምግብ ዋስትናንና የማይበገር የግብርና ስርዓት መገንባትን ዓላማ ያደረጉ ናቸው ብለዋል።
አፍሪካውያን የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ለመስኖ ልማት፣ ለግብርና ኢንቨስትመንት፣ ለቴክኖሎጂና ለመረጃ ጥራት ትኩረት እንዲሰጡም ጠይቀዋል።
አፍሪካውያን በጋራ ከሰሩ ርሃብን ማስወገድ፣ የአየር ንብረት ለውጥን በብቃት መቋቋምና የትውልዱን የብልፅግና መሻትን ማሳካት እንደሚችሉ ተናግረዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026