ሽረ እንዳስላሴ የካቲት 05/2017 (ኢዜአ)- የአክሱም ዩኒቨርሲቲ በጥናት ያገኛቸውን የምርምር ውጤቶች አገልግሎት ላይ እንዲውሉ እየሰራ መሆኑን አስታወቀ።
በአክሱም ዩኒቨርሲቲ የሽረ እንዳስላሴ ካምፓስ ኃላፊ ዳዊት ማሞ (ዶ/ር)፤ ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማሩ ባለፈ ማህበራዊ አገልግሎቱን እየተወጣና ችግር ፈች የምርምር ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
በምርምር ስራዎቹ አነስተኛ የወርቅ ማጠቢያ መሳሪያና አደገኛ አረምን ወደ ከሰል የሚቀይር አዲስ የፈጠራ ውጤት ይፋ አድርጓል።
በዚህም በምርምር የተገኘው የወርቅ ማጠቢያ ማሽን በሰው ጉልበት ሲከናወን የቆየውን የወርቅ ማእድን ከአፈር የመለየት እና የማጠብ ስራ ፈጣንና ቀልጣፋ የሚያደርግ ስለመሆኑ ሃላፊው አንስተዋል።
የማሽኑ አገልግሎት ከፍተኛ በመሆኑ በአንድ ሰዓት ከግማሽ ኩንታል አፈር ውስጥ ያለምንም ብክነት የወርቅ ማእድንን መለየትና ማጠብ ያስችላል ብለዋል።
በተለያዩ አካባቢዎች የሚስተዋለውን አደገኛ አረም በኬሚካል ወደ ከሰል ምርትነት መለወጥ የሚያስችል ግኝትም ሌላኛው የዩኒቨርሲቲው ውጤት መሆኑን አንስተዋል።
እነዚህ ፈጠራዎች በሙከራ ደረጃ ውጤታማ መሆናቸውን አስታውሰው በቀጣይ ለህብረተሰቡ አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ እንቅስቃሴ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።
በቀጣይም የአፈርን ለምነት ለመጠበቅ የሚያስችል ''ቨርሚንግ'' የተባለ ኮምፖስት ለማምረት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ዶ/ር ዳዊት ተናግረዋል።
የምርምር ስራዎቹ በዩኒቨርሲቲው እውቅና የተሰጣቸው መሆኑን ጠቅሰው በቀጣይ በህብርተሰቡ ዘንድ ጥቅም ላይ ለማዋል ይሰራል ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025