
ሽረ እንዳስላሴ የካቲት 05/2017 (ኢዜአ)- የአክሱም ዩኒቨርሲቲ በጥናት ያገኛቸውን የምርምር ውጤቶች አገልግሎት ላይ እንዲውሉ እየሰራ መሆኑን አስታወቀ።
በአክሱም ዩኒቨርሲቲ የሽረ እንዳስላሴ ካምፓስ ኃላፊ ዳዊት ማሞ (ዶ/ር)፤ ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማሩ ባለፈ ማህበራዊ አገልግሎቱን እየተወጣና ችግር ፈች የምርምር ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
በምርምር ስራዎቹ አነስተኛ የወርቅ ማጠቢያ መሳሪያና አደገኛ አረምን ወደ ከሰል የሚቀይር አዲስ የፈጠራ ውጤት ይፋ አድርጓል።
በዚህም በምርምር የተገኘው የወርቅ ማጠቢያ ማሽን በሰው ጉልበት ሲከናወን የቆየውን የወርቅ ማእድን ከአፈር የመለየት እና የማጠብ ስራ ፈጣንና ቀልጣፋ የሚያደርግ ስለመሆኑ ሃላፊው አንስተዋል።
የማሽኑ አገልግሎት ከፍተኛ በመሆኑ በአንድ ሰዓት ከግማሽ ኩንታል አፈር ውስጥ ያለምንም ብክነት የወርቅ ማእድንን መለየትና ማጠብ ያስችላል ብለዋል።
በተለያዩ አካባቢዎች የሚስተዋለውን አደገኛ አረም በኬሚካል ወደ ከሰል ምርትነት መለወጥ የሚያስችል ግኝትም ሌላኛው የዩኒቨርሲቲው ውጤት መሆኑን አንስተዋል።
እነዚህ ፈጠራዎች በሙከራ ደረጃ ውጤታማ መሆናቸውን አስታውሰው በቀጣይ ለህብረተሰቡ አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ እንቅስቃሴ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።
በቀጣይም የአፈርን ለምነት ለመጠበቅ የሚያስችል ''ቨርሚንግ'' የተባለ ኮምፖስት ለማምረት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ዶ/ር ዳዊት ተናግረዋል።
የምርምር ስራዎቹ በዩኒቨርሲቲው እውቅና የተሰጣቸው መሆኑን ጠቅሰው በቀጣይ በህብርተሰቡ ዘንድ ጥቅም ላይ ለማዋል ይሰራል ብለዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026