የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>የአክሱም ዩኒቨርሲቲ በጥናት ያገኛቸውን የምርምር ውጤቶች አገልግሎት ላይ እንዲውሉ እየሰራ ነው</p>

Feb 13, 2025

IDOPRESS

ሽረ እንዳስላሴ የካቲት 05/2017 (ኢዜአ)- የአክሱም ዩኒቨርሲቲ በጥናት ያገኛቸውን የምርምር ውጤቶች አገልግሎት ላይ እንዲውሉ እየሰራ መሆኑን አስታወቀ።

በአክሱም ዩኒቨርሲቲ የሽረ እንዳስላሴ ካምፓስ ኃላፊ ዳዊት ማሞ (ዶ/ር)፤ ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማሩ ባለፈ ማህበራዊ አገልግሎቱን እየተወጣና ችግር ፈች የምርምር ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

በምርምር ስራዎቹ አነስተኛ የወርቅ ማጠቢያ መሳሪያና አደገኛ አረምን ወደ ከሰል የሚቀይር አዲስ የፈጠራ ውጤት ይፋ አድርጓል።

በዚህም በምርምር የተገኘው የወርቅ ማጠቢያ ማሽን በሰው ጉልበት ሲከናወን የቆየውን የወርቅ ማእድን ከአፈር የመለየት እና የማጠብ ስራ ፈጣንና ቀልጣፋ የሚያደርግ ስለመሆኑ ሃላፊው አንስተዋል።

የማሽኑ አገልግሎት ከፍተኛ በመሆኑ በአንድ ሰዓት ከግማሽ ኩንታል አፈር ውስጥ ያለምንም ብክነት የወርቅ ማእድንን መለየትና ማጠብ ያስችላል ብለዋል።

በተለያዩ አካባቢዎች የሚስተዋለውን አደገኛ አረም በኬሚካል ወደ ከሰል ምርትነት መለወጥ የሚያስችል ግኝትም ሌላኛው የዩኒቨርሲቲው ውጤት መሆኑን አንስተዋል።

እነዚህ ፈጠራዎች በሙከራ ደረጃ ውጤታማ መሆናቸውን አስታውሰው በቀጣይ ለህብረተሰቡ አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ እንቅስቃሴ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።

በቀጣይም የአፈርን ለምነት ለመጠበቅ የሚያስችል ''ቨርሚንግ'' የተባለ ኮምፖስት ለማምረት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ዶ/ር ዳዊት ተናግረዋል።

የምርምር ስራዎቹ በዩኒቨርሲቲው እውቅና የተሰጣቸው መሆኑን ጠቅሰው በቀጣይ በህብርተሰቡ ዘንድ ጥቅም ላይ ለማዋል ይሰራል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026