
ሽረ እንዳስላሴ የካቲት 05/2017 (ኢዜአ)- የአክሱም ዩኒቨርሲቲ በጥናት ያገኛቸውን የምርምር ውጤቶች አገልግሎት ላይ እንዲውሉ እየሰራ መሆኑን አስታወቀ።
በአክሱም ዩኒቨርሲቲ የሽረ እንዳስላሴ ካምፓስ ኃላፊ ዳዊት ማሞ (ዶ/ር)፤ ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማሩ ባለፈ ማህበራዊ አገልግሎቱን እየተወጣና ችግር ፈች የምርምር ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
በምርምር ስራዎቹ አነስተኛ የወርቅ ማጠቢያ መሳሪያና አደገኛ አረምን ወደ ከሰል የሚቀይር አዲስ የፈጠራ ውጤት ይፋ አድርጓል።
በዚህም በምርምር የተገኘው የወርቅ ማጠቢያ ማሽን በሰው ጉልበት ሲከናወን የቆየውን የወርቅ ማእድን ከአፈር የመለየት እና የማጠብ ስራ ፈጣንና ቀልጣፋ የሚያደርግ ስለመሆኑ ሃላፊው አንስተዋል።
የማሽኑ አገልግሎት ከፍተኛ በመሆኑ በአንድ ሰዓት ከግማሽ ኩንታል አፈር ውስጥ ያለምንም ብክነት የወርቅ ማእድንን መለየትና ማጠብ ያስችላል ብለዋል።
በተለያዩ አካባቢዎች የሚስተዋለውን አደገኛ አረም በኬሚካል ወደ ከሰል ምርትነት መለወጥ የሚያስችል ግኝትም ሌላኛው የዩኒቨርሲቲው ውጤት መሆኑን አንስተዋል።
እነዚህ ፈጠራዎች በሙከራ ደረጃ ውጤታማ መሆናቸውን አስታውሰው በቀጣይ ለህብረተሰቡ አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ እንቅስቃሴ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።
በቀጣይም የአፈርን ለምነት ለመጠበቅ የሚያስችል ''ቨርሚንግ'' የተባለ ኮምፖስት ለማምረት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ዶ/ር ዳዊት ተናግረዋል።
የምርምር ስራዎቹ በዩኒቨርሲቲው እውቅና የተሰጣቸው መሆኑን ጠቅሰው በቀጣይ በህብርተሰቡ ዘንድ ጥቅም ላይ ለማዋል ይሰራል ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026