
አዲስ አበባ፤ የካቲት 06/2017(ኢዜአ)፦በአፍሪካ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ግብርናን በመገንባት ከተረጂነት የተላቀቀ ማህበረሰብ ለመፍጠር አባል አገራቱ በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ የአፍሪካ ሕብረት ገለፀ።
ትናንት የተጀመረው 46ኛው የአፍሪካ ህብረት የሥራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ በሁለተኛ ቀን ውሎው በተለያዩ ጉዳዮች ላይ እየመከረ ነው።
ስብሰባው "የማካካሻ ፍትሕ ለአፍሪካውያንና ዘርዓ-አፍሪካውያን” በሚል መሪ ሃሳብ እየተካሄደ ይገኛል ።
በህብረቱ የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የብሉ ኢኮኖሚና የዘላቂ የአካባቢ ልማት ኮሚሽነር አምባሳደር ጆሴፋ ሳኮ በሰጡት መግለጫ በአፍሪካ ዘመናዊ ግብርና በመገንባት ሕዝቦቿን ከተረጂነት ማላቀቅ ያስፈልጋል ብለዋል።
ድርቅን ጨምሮ የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎችን መቋቋም የሚችል የግብርና አሰራር ለመተግበር የተጀመሩ ሥራዎች ሊጠናከሩ ይገባል ሲሉ አሳስበዋል።
በዚህም ኮሚሽኑ የተለያዩ የስትራቴጂ እና የድርጊት መርኃ ግብሮችን ቀርጾ እየተገበረ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።
በአፍሪካ ከእርዳታ ጥገኝነት የወጣ ማህበረሰብ ለመፍጠር ሁሉም አገራት በትብብር ሊሰሩ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።
ለዚህ ስኬት ዘላቂ የግብርና ልማት ሥራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡
እንደ አውሮፓውያኑ ዘመን አቆጣጣር 2050 የአህጉሪቱ ህዝብ 2 ነጥብ 5 ቢሊየን ይደርሳል ተብሎ መገመቱን ጠቅሰው ለህብረተሰቡ በቂ ምርት ለማቅረብ ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድግ የግብርና አሰራር መተግበር እንደሚገባ ነው ያስታወቁት፡፡
የግብርና ኢንቨስትመንትን በማሳደግና በፋይናንስ በመደገፍ የዘርፉን ዕድገት ለማሳለጥ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ነው ያሳሰቡት።
በዚህም ግቡን ለማሳካት የሚያስችሉ ሥራዎች መጀመራቸውን ጠቅሰው በአፍሪካ በምግብ ሰብል ራስን ለመቻል የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል ሲሉ ጠቁመዋል።
የምግብና ሥርዓተ ምግብ አጠቃቀምን በማሻሻል ዜጎች የተመጣጠነ ምግብ እንዲያገኙ የተጀመሩ ተግባራት ይበልጥ መጠናከር አለባቸው ብለዋል።
በአህጉሪቱ ከ70 በመቶ በላይ የሚሆነው ህዝብ በገጠር እንደሚኖርና መተዳደሪያውም በግብርና ላይ የተመሠረተ በመሆኑ አገራት ይህን ታሳቢ ያደረጉ ሥራዎችን ሊሰሩ አንደሚገባ ነው ያሳሰቡት።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026