የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

<p>አህጉራዊ የፋይናንስ ውህደትን ለማሳደግ የሚያስችል የትብብር ስምምነት ተፈረመ</p>

Feb 17, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፣የካቲት 9/2017 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለንዋዮች ገበያና የርዋንዳው ስቶክ ኤክስቼንጅ አህጉራዊ የፋይናንስ ውህደትን ለማሳደግ የሚያስችል የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል።

ስምምነቱን የኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለንዋዮች ገበያ ዋና ስራ አስፈፃሚ ጥላሁን እስማዔል (ዶ/ር) እና የሩዋንዳ ስቶክ ኤክስቸንጅ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ፒየር ሴሌስቲን ራባቡኩምባ ተፈራርመዋል፡፡

ስምምነቱ ትብብርን ለማጎልበት፣ እውቀትን ለመለዋወጥ እና አህጉራዊ የፋይናንስ ውህደትን ለማሳደግ እንደሚያስችል ተገልጿል፡፡

የተቋማቱ ስልታዊ አጋርነት የገበያ ልማትን ለማጎልበት፣ የአቅም ግንባታን ለማሳደግ እና በሁለቱ ገበያዎች አዳዲስ የኢንቨስትመንት እድሎችን ለመፍጠር ያለመ ነው ተብሏል።

በተጨማሪም የርዋንዳ ስቶክ ኤክስቼንጅን የካበተ ልምድ በመጠቀም በሁለቱ ሀገራት ያሉ የካፒታል ገበያዎችን ውሕደት እንደሚያጠናክር ተጠቁሟል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025