አዲስ አበባ፣የካቲት 9/2017 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለንዋዮች ገበያና የርዋንዳው ስቶክ ኤክስቼንጅ አህጉራዊ የፋይናንስ ውህደትን ለማሳደግ የሚያስችል የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል።
ስምምነቱን የኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለንዋዮች ገበያ ዋና ስራ አስፈፃሚ ጥላሁን እስማዔል (ዶ/ር) እና የሩዋንዳ ስቶክ ኤክስቸንጅ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ፒየር ሴሌስቲን ራባቡኩምባ ተፈራርመዋል፡፡
ስምምነቱ ትብብርን ለማጎልበት፣ እውቀትን ለመለዋወጥ እና አህጉራዊ የፋይናንስ ውህደትን ለማሳደግ እንደሚያስችል ተገልጿል፡፡
የተቋማቱ ስልታዊ አጋርነት የገበያ ልማትን ለማጎልበት፣ የአቅም ግንባታን ለማሳደግ እና በሁለቱ ገበያዎች አዳዲስ የኢንቨስትመንት እድሎችን ለመፍጠር ያለመ ነው ተብሏል።
በተጨማሪም የርዋንዳ ስቶክ ኤክስቼንጅን የካበተ ልምድ በመጠቀም በሁለቱ ሀገራት ያሉ የካፒታል ገበያዎችን ውሕደት እንደሚያጠናክር ተጠቁሟል፡፡
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025