
አዲስ አበባ፣የካቲት 9/2017 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለንዋዮች ገበያና የርዋንዳው ስቶክ ኤክስቼንጅ አህጉራዊ የፋይናንስ ውህደትን ለማሳደግ የሚያስችል የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል።
ስምምነቱን የኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለንዋዮች ገበያ ዋና ስራ አስፈፃሚ ጥላሁን እስማዔል (ዶ/ር) እና የሩዋንዳ ስቶክ ኤክስቸንጅ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ፒየር ሴሌስቲን ራባቡኩምባ ተፈራርመዋል፡፡
ስምምነቱ ትብብርን ለማጎልበት፣ እውቀትን ለመለዋወጥ እና አህጉራዊ የፋይናንስ ውህደትን ለማሳደግ እንደሚያስችል ተገልጿል፡፡
የተቋማቱ ስልታዊ አጋርነት የገበያ ልማትን ለማጎልበት፣ የአቅም ግንባታን ለማሳደግ እና በሁለቱ ገበያዎች አዳዲስ የኢንቨስትመንት እድሎችን ለመፍጠር ያለመ ነው ተብሏል።
በተጨማሪም የርዋንዳ ስቶክ ኤክስቼንጅን የካበተ ልምድ በመጠቀም በሁለቱ ሀገራት ያሉ የካፒታል ገበያዎችን ውሕደት እንደሚያጠናክር ተጠቁሟል፡፡
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026