
አዲስ አበባ፤ የካቲት 11/2017(ኢዜአ)፦ በፀጥታና ደህንነት በኢኮኖሚና በፖለቲካው መስክ የተከናወኑ ተግባራት ሀገር አሻጋሪ መሆናቸውን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።
የጠቅላይ ሚኒስትር ተጠሪ ተቋማት የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያው አጋማሽ አፈጻጸም የግምገማ መድረክ እየተካሄደ ነው።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በመክፈቻ ንግግራቸው፥ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያው አጋማሽ በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚና ሌሎችም መስኮች በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል።
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የለውጡ መንግሥት ከተመሠረተ በአጭር ጊዜ ውስጥ የላቁ ተግባራትን ማከናወኑንም ጠቅሰዋል።

በተለይም በፀጥታና ደህንነት በኢኮኖሚና በፖለቲካው መስክ የተከናወኑ ተግባራት ሀገር አሻጋሪ ናቸው ብለዋል።
ብዙ ፈተናዎች ቢገጥሙንም እየተሻገርናቸው ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ በቀጣይም ፈተናዎችን ለተሻገረ ድል መትጋት ወሳኝ ነው ብለዋል።
በግማሽ ዓመቱ ከልማት ሥራዎች ባሻገር በርካታ ሀገራዊ፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ሁነቶችንና ጉባኤዎችን ማስተናገድ መቻሉንም ተናግረዋል።
የኢትዮጵያን ገፅታ የቀየሩና ስሟን በበጎ ያስጠሩ ስራዎች መከናወናቸውን በማንሳት፥ በዓመቱ በዓለም ከፍተኛ የቱሪስት መዳረሻ ከሆኑ ሀገራት አንዷ ሆናለች ብለዋል።
በድህነትና ኋላቀርነት ትታወቅ የነበረችው ሀገራችን ዓይን ገላጭ ሥራዎችን በመተግበር በበርካታ መስኮች አስደማሚ ለውጥ አምጥታለች ብለዋል።

ለተገኙ ተስፋ ሰጪ ስኬቶች የጠቅላይ ሚኒስትር ተጠሪ ተቋማት የመሪነት ድርሻቸው የላቀ እንደሆነም ገልጸዋል።
የእስካሁን ሥራዎች ጅምር እንጂ የተሟላ የስኬት ደረጃ ላይ አልደረሱም ያሉት አቶ ተመስገን፥ የዓለም ነባራዊ ሁኔታን ታሳቢ ያደረገ ሥራ ከፊታችን ይጠብቀናል ብለዋል።
ኢትዮጵያ በሁሉም መስክ ራሷን እንድትችል እና በአፍሪካ የብልፅግና ተምሳሌት እንድትሆን የተቀናጀና እረፍት የለሽ ሥራ የግድ መሆኑን ጠቅሰዋል።
የጠቅላይ ሚኒስትር ተጠሪ ተቋማት ከራሳቸው ባለፈ ለሌሎች ተቋማት ግብ መሳካት ጉልህ አስተዋፅኦ ማበርከት እንዳለባቸውም ገልፀዋል።
በተለይ አገልግሎት አሰጣጥን ማዘመን፣ ወጪ ቆጣቢ መሆን፣ ቅንጅታዊ አሠራርን ማጠናከር እና ተፅዕኖ መፍጠር ላይ ተጠሪ ተቋማቱ የትኩረት ማዕከል መሆን አለባቸው ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026