
አዲስ አበባ፤ የካቲት 11/2017(ኢዜአ)፦ በፀጥታና ደህንነት በኢኮኖሚና በፖለቲካው መስክ የተከናወኑ ተግባራት ሀገር አሻጋሪ መሆናቸውን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።
የጠቅላይ ሚኒስትር ተጠሪ ተቋማት የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያው አጋማሽ አፈጻጸም የግምገማ መድረክ እየተካሄደ ነው።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በመክፈቻ ንግግራቸው፥ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያው አጋማሽ በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚና ሌሎችም መስኮች በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል።
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የለውጡ መንግሥት ከተመሠረተ በአጭር ጊዜ ውስጥ የላቁ ተግባራትን ማከናወኑንም ጠቅሰዋል።

በተለይም በፀጥታና ደህንነት በኢኮኖሚና በፖለቲካው መስክ የተከናወኑ ተግባራት ሀገር አሻጋሪ ናቸው ብለዋል።
ብዙ ፈተናዎች ቢገጥሙንም እየተሻገርናቸው ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ በቀጣይም ፈተናዎችን ለተሻገረ ድል መትጋት ወሳኝ ነው ብለዋል።
በግማሽ ዓመቱ ከልማት ሥራዎች ባሻገር በርካታ ሀገራዊ፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ሁነቶችንና ጉባኤዎችን ማስተናገድ መቻሉንም ተናግረዋል።
የኢትዮጵያን ገፅታ የቀየሩና ስሟን በበጎ ያስጠሩ ስራዎች መከናወናቸውን በማንሳት፥ በዓመቱ በዓለም ከፍተኛ የቱሪስት መዳረሻ ከሆኑ ሀገራት አንዷ ሆናለች ብለዋል።
በድህነትና ኋላቀርነት ትታወቅ የነበረችው ሀገራችን ዓይን ገላጭ ሥራዎችን በመተግበር በበርካታ መስኮች አስደማሚ ለውጥ አምጥታለች ብለዋል።

ለተገኙ ተስፋ ሰጪ ስኬቶች የጠቅላይ ሚኒስትር ተጠሪ ተቋማት የመሪነት ድርሻቸው የላቀ እንደሆነም ገልጸዋል።
የእስካሁን ሥራዎች ጅምር እንጂ የተሟላ የስኬት ደረጃ ላይ አልደረሱም ያሉት አቶ ተመስገን፥ የዓለም ነባራዊ ሁኔታን ታሳቢ ያደረገ ሥራ ከፊታችን ይጠብቀናል ብለዋል።
ኢትዮጵያ በሁሉም መስክ ራሷን እንድትችል እና በአፍሪካ የብልፅግና ተምሳሌት እንድትሆን የተቀናጀና እረፍት የለሽ ሥራ የግድ መሆኑን ጠቅሰዋል።
የጠቅላይ ሚኒስትር ተጠሪ ተቋማት ከራሳቸው ባለፈ ለሌሎች ተቋማት ግብ መሳካት ጉልህ አስተዋፅኦ ማበርከት እንዳለባቸውም ገልፀዋል።
በተለይ አገልግሎት አሰጣጥን ማዘመን፣ ወጪ ቆጣቢ መሆን፣ ቅንጅታዊ አሠራርን ማጠናከር እና ተፅዕኖ መፍጠር ላይ ተጠሪ ተቋማቱ የትኩረት ማዕከል መሆን አለባቸው ብለዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026