አዲስ አበባ፤ የካቲት 12/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያና ሩሲያ ጋር ያላቸውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ይበልጥ ለማሳደግ ቁርጠኛ መሆናቸውን ገለፁ።
በኢትዮጵያ መንግስት እና በሩሲያ መንግስት የመጀመሪያው የኒውክለር ቴክኖሎጂ ፍኖተ ካርታ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ መደረጉን ተከትሎ ለመጪዎቹ 3 ዓመታት የሚያገለግል ሁለተኛው ፍኖተ ካርታ በዛሬው ዕለት ተፈርሟል።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ኢትዮጵያ እና ሩስያ በኢኮኖሚያዊ ትብብር፣ በባህል ልውውጥ፣ በቴክኖሎጂ ፈጠራዎችና ሽግግር፣ በኢንቨስትመንት፣ በትምህርት፣ በግብርና በንግድ ልውውጥ እና በመሰረተ ልማት ዝርጋታ ዘርፎች ላይ ይበልጥ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ያለመ የምክክር መድረክ አካሂደዋል።
የምክክር መድረኩ ዓላማ የኢትዮጵያና የሩስያ የሁለትዮሽ ግንኙነትን ከመቼውም በላይ ከፍ በማድረግ የጋራ ስምምነቶችን ለመፍጠር ያለመ ነው።
ከኢትዮጵያ በኩል የኢትዮ-ሩሲያ የበይነ መንግስታቱ የጋራ ኮሚቴ ጣምራ ሰብሳቢ የሆኑት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር) ኢትዮጵያ ከሩሲያ ፌዴሬሽን ጋር የምትጋራውን ለዘመናት ያስቆጠረ እና ታሪካዊ ግንኙነትን ከፍ ለማድረግ እየተደረገ ያለው ጥረት እጅግ ፍሬማ ነው ብለዋል።
ከዚህ በፊት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በሩሲያ ያደረጉት ጉብኝት የሀገራቱን ግንኙነትን በማጠናከር የጋራ መግባባትና አጋርነት ማሳደጉን ገልፀዋል።
በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለው ወዳጅነት የዘመናት ግንኙነት ውጤት ነው ያሉት ሚኒስትሩ፤ የምናከናውናቸው የአጋር ስምምነቶች የዛሬውን አንገብጋቢ ጉዳዮች ከማንሳት ባለፈ ለቀጣይ ትውልዶች ጸንቶ የሚዘልቅና የሚለመልም አጋርነት መሰረት የሚጥል መሆኑን አስገንዝበዋል።
ከሩሲያ በኩል የበይነ_መንግስታት የጋራ ኮሚቴው ጣምራ ሰብሳቢ የሆኑት የኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትሩ ማክሲም ሬሽቴንኮቭ በበኩላቸው ሩሲያ ከኢትዮጵያ ጋር በአጋርነት ሰፊ ሰራዎች እየሰራች መሆኑን ጠቁመዋል።
በቀጣይም ግንኙነቱን ይበልጥ በማጠናከርና በመቀራረብ ዘርፈ ብዙ ስራዎች ለመስራት ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላቸውም መግለፃቸውን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
በመሆኑም በንግድ፣ በጤና፣ በባንክ ስርዓት፣ በኢነርጂ፣ በቴክኖሎጂ፣ በማስ ሚዲያ፣ በቱሪዝምና ንግድ በሌሎችም ዘርፎች ለመስራት በጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እንደሚተጉ አረጋግጠዋል።
በምክክሩ ላይ የጤና፣ የቱሪዝም፣ የንግድና ቀጠናዊ ትስስር፣ የትምህርት፣ የውጪ ጉዳይ፣ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች እና የሌሎች ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች ተሳትፈዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025