
አዲስ አበባ፤ የካቲት 12/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያና ሩሲያ ጋር ያላቸውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ይበልጥ ለማሳደግ ቁርጠኛ መሆናቸውን ገለፁ።
በኢትዮጵያ መንግስት እና በሩሲያ መንግስት የመጀመሪያው የኒውክለር ቴክኖሎጂ ፍኖተ ካርታ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ መደረጉን ተከትሎ ለመጪዎቹ 3 ዓመታት የሚያገለግል ሁለተኛው ፍኖተ ካርታ በዛሬው ዕለት ተፈርሟል።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ኢትዮጵያ እና ሩስያ በኢኮኖሚያዊ ትብብር፣ በባህል ልውውጥ፣ በቴክኖሎጂ ፈጠራዎችና ሽግግር፣ በኢንቨስትመንት፣ በትምህርት፣ በግብርና በንግድ ልውውጥ እና በመሰረተ ልማት ዝርጋታ ዘርፎች ላይ ይበልጥ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ያለመ የምክክር መድረክ አካሂደዋል።

የምክክር መድረኩ ዓላማ የኢትዮጵያና የሩስያ የሁለትዮሽ ግንኙነትን ከመቼውም በላይ ከፍ በማድረግ የጋራ ስምምነቶችን ለመፍጠር ያለመ ነው።
ከኢትዮጵያ በኩል የኢትዮ-ሩሲያ የበይነ መንግስታቱ የጋራ ኮሚቴ ጣምራ ሰብሳቢ የሆኑት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር) ኢትዮጵያ ከሩሲያ ፌዴሬሽን ጋር የምትጋራውን ለዘመናት ያስቆጠረ እና ታሪካዊ ግንኙነትን ከፍ ለማድረግ እየተደረገ ያለው ጥረት እጅግ ፍሬማ ነው ብለዋል።
ከዚህ በፊት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በሩሲያ ያደረጉት ጉብኝት የሀገራቱን ግንኙነትን በማጠናከር የጋራ መግባባትና አጋርነት ማሳደጉን ገልፀዋል።
በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለው ወዳጅነት የዘመናት ግንኙነት ውጤት ነው ያሉት ሚኒስትሩ፤ የምናከናውናቸው የአጋር ስምምነቶች የዛሬውን አንገብጋቢ ጉዳዮች ከማንሳት ባለፈ ለቀጣይ ትውልዶች ጸንቶ የሚዘልቅና የሚለመልም አጋርነት መሰረት የሚጥል መሆኑን አስገንዝበዋል።

ከሩሲያ በኩል የበይነ_መንግስታት የጋራ ኮሚቴው ጣምራ ሰብሳቢ የሆኑት የኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትሩ ማክሲም ሬሽቴንኮቭ በበኩላቸው ሩሲያ ከኢትዮጵያ ጋር በአጋርነት ሰፊ ሰራዎች እየሰራች መሆኑን ጠቁመዋል።
በቀጣይም ግንኙነቱን ይበልጥ በማጠናከርና በመቀራረብ ዘርፈ ብዙ ስራዎች ለመስራት ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላቸውም መግለፃቸውን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።

በመሆኑም በንግድ፣ በጤና፣ በባንክ ስርዓት፣ በኢነርጂ፣ በቴክኖሎጂ፣ በማስ ሚዲያ፣ በቱሪዝምና ንግድ በሌሎችም ዘርፎች ለመስራት በጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እንደሚተጉ አረጋግጠዋል።
በምክክሩ ላይ የጤና፣ የቱሪዝም፣ የንግድና ቀጠናዊ ትስስር፣ የትምህርት፣ የውጪ ጉዳይ፣ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች እና የሌሎች ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች ተሳትፈዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026