
ጊምቢ፤ የካቲት 12/2017(ኢዜአ)፡- ደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ አንድ ሚሊዮን የሚሆኑ ዝርያቸው የተሻሻለ የቡና ችግኞችን ለአርሶ አደሮች ለማሰራጨት መዘጋጀቱን አስታወቀ።

በዩኒቨርሲቲው የተቀናጀ ግብርና ምርምር ማዕክል ዳይሬክተር ሶሬሳ ሹማ፤ ለኢዜአ እንደገለጹት ዩኒቨርሲቲው ከጅማና ሌሎች ግብርና ምርምር ማዕከላት በምርምር የተገኙ 12 አይነት የቡና ዝርያዎችን በማላመድና በማባዛት በመጪው ግንቦት ወር ለአርሶ አደሮች ለማሰራጨት ተዘጋጅቷል።
ለስርጭትየተዘጋጁት የቡና ችግኝ ዝርያዎች በሽታን ተቋቁመው በሄክታር ከ14 ኩንታል በላይ ምርት የሚሰጡ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የቡና ዝርያዎቹ ከ2 እስከ 3 ዓመት ጊዜ ውስጥ ምርት የሚሰጡ መሆናቸውንም አመልክተዋል።
የቡና ችግኞቹ በቄለምና በምዕራብ ወለጋ ዞኖች ለሚገኙ ቡና አምራች አርሶ አደሮች እንደሚሰራጩ አስታውቀዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026