
ጊምቢ፤ የካቲት 12/2017(ኢዜአ)፡- ደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ አንድ ሚሊዮን የሚሆኑ ዝርያቸው የተሻሻለ የቡና ችግኞችን ለአርሶ አደሮች ለማሰራጨት መዘጋጀቱን አስታወቀ።

በዩኒቨርሲቲው የተቀናጀ ግብርና ምርምር ማዕክል ዳይሬክተር ሶሬሳ ሹማ፤ ለኢዜአ እንደገለጹት ዩኒቨርሲቲው ከጅማና ሌሎች ግብርና ምርምር ማዕከላት በምርምር የተገኙ 12 አይነት የቡና ዝርያዎችን በማላመድና በማባዛት በመጪው ግንቦት ወር ለአርሶ አደሮች ለማሰራጨት ተዘጋጅቷል።
ለስርጭትየተዘጋጁት የቡና ችግኝ ዝርያዎች በሽታን ተቋቁመው በሄክታር ከ14 ኩንታል በላይ ምርት የሚሰጡ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የቡና ዝርያዎቹ ከ2 እስከ 3 ዓመት ጊዜ ውስጥ ምርት የሚሰጡ መሆናቸውንም አመልክተዋል።
የቡና ችግኞቹ በቄለምና በምዕራብ ወለጋ ዞኖች ለሚገኙ ቡና አምራች አርሶ አደሮች እንደሚሰራጩ አስታውቀዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026