የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>የክልሉን ሃብትና ጸጋ በመለየት ለዜጎች   የሥራ እድል መፍጠር  የሁልጊዜ ተግባራችን ነው - አህመዲን መሐመድ(ዶ/ር)</p>

Feb 20, 2025

IDOPRESS

ደሴ ፤ የካቲት 12/2017(ኢዜአ)፡ -የአማራ ክልልን ሃብትና ጸጋ በመለየት ለዜጎች የሥራ እድል መፍጠር የሁልጊዜ ተግባራችን ነው ሲሉ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ከተሞች ልማት ክላስተር አስተባባሪና የከተማና መሰረት ልማት ቢሮ ኃላፊ አህመዲን መሐመድ (ዶ/ር)ገለጹ።

የክልሉ ሥራና ስልጠና ቢሮ የ2017 በጀት ዓመት የስድስት ወራት ሥራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ በኮምቦልቻ ከተማ እየተካሄደ ነው።


በመድረኩ ላይ የተገኙት አህመዲን መሐመድ(ዶ/ር) እንደተናገሩት፤ በክልሉ ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረገ የሥራ እድል ፈጠራና የእውቀት ሽግግርን ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው።

በዚህም በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች ያለውን ሃብትና ጸጋ በመለየት ለዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ እድል መፍጠር የሁልጊዜ ተግባራችን ነው ብለዋል።

ሰላምና የሥራ እድል የማይነጣጠሉ የክልሉ የትኩረት አጀንዳዎች መሆናቸውን ጠቅሰው፤ በግማሽ በጀት ዓመቱ በዚህ ተግባር ላይ በመረባረብ አበረታች ውጤት መስመዝገብ መቻሉን ገልጸዋል።

በኮደርስ ስልጠና፣ በኮሪደርና ኢንዱስትሪ ልማት ላይ ወጣቱን በማሰማራት በቴክኖሎጂ የበቃና ተወዳዳሪ የሰው ሀይል ለመገንባት ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት ይኖርብናል ብለዋል።


የአማራ ክልል ሥራና ስልጠና ቢሮ ኃላፊ ስቡህ ገበያው(ዶ/ር) በበኩላቸው ፤ በክልሉ የሥራ እድል መፍጠሪያ ፀጋዎችን በመለየት ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህም በቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅች በአጭር፣ በመካከለኛና በረጅም ጊዜ ስልጠና በመስጠት በበጀት ዓመቱ ከታቀደው ውስጥ ባለፉት ሰባት ወራት ከ500 ሺህ ለሚበልጡ ሰዎች በተለያዩ የስራ መስኮች የሥራ እድል መፍጠር መቻሉን ገልጸዋል

የብድር፣ የመስሪያና የመሸጫ ቦታ፣ የገበያ ትስስር በመፍጠር ኢንተርፕራይዞችን ወደ ባለሃብትነት እንዲሸጋገሩና ተጨማሪ የሥራ እድል እንዲፈጥሩ ድጋፍ እየተደረገ ነው ብለዋል።


በከተማው ለዜጎች የሥራ እድል በመፍጠር ኢኮኖሚውን ለማነቃቃት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ይገኛል ያሉት የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ መሀመድአሚን የሱፍ ናቸው።

ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት በሚቆየው መድረክ የክልል፣ የዞን፣ የከተማና የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች አመራር አባላትና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026