የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>በመዲናዋ ባለፉት ስድስት ወራት በሰው ተኮርና በጎ ፈቃድ አገልግሎት ከ 1 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል -ከንቲባ አዳነች አቤቤ</p>

Feb 20, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 12/2017(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ በ2017 በጀት ዓመት ስድስት ወራት በሰው ተኮርና በጎ ፈቃድ አገልግሎት 1 ሚሊዮን 197 ሺህ 413 ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናገሩ።

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 4ኛ የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ጉባኤ ተካሂዷል።


ከንቲባ አዳነች በመዲናዋ ባለፉት ስድስት ወራት በየዘርፉ የተያዙ እቅዶችን አፈጻጸም ለምክር ቤቱ አቅርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።

በዚህም የበጎ ፍቃድና ሰው ተኮር አገልግሎት ለዘላቂ ልማት የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ ለማሳደግ በተከናወኑ ተግባራት የዜጎችን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ውጤቶች ተገኝተዋል ብለዋል።

በመዲናዋ የተለያዩ ቦታዎች በተቋቋሙ 24 የተስፋ ብርሃን የምገባ ማዕከላት በየቀኑ 36 ሺህ ለሚደርሱ ወገኖች የምገባ መርሃ ግብር እየተከናወነ መሆኑንም ጠቁመዋል።

እንዲሁም በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ ዜጎች፣ አረጋዊያን፣አቅመ ደካሞች፣ የአገር ባለውለታዎችን ጨምሮ 3 ሺህ 737 ቤቶችን በመገንባት 20 ሺህ 484 ቤተሰቦችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉንም አመልክተዋል።

ከቤት ልማት አኳያም በመንግሥት አስተባባሪነት፣ በግል አልሚዎችና በሪል ስቴት አማራጮች 27 ሺህ 304 ቤቶች መገንባታቸውንም ጠቅሰዋል።

በበጀት ዓመቱ ግማሽ ዓመት ሁለተኛው የኮሪደር ልማት ሥራ ስኬታማ በሆነ መልኩ መከናወኑን ያነሱ ሲሆን በኮሪደር ልማት ምክንያት ለሚነሱ ዜጎችና የንግድ ተቋማት ምትክ ቦታ መሰጠቱን ተናግረዋል።

ለልማት ተነሺዎች የመኖሪያ ቤቶች እንዲሁም መሥሪያ ሼዶች ተደራሽ መደረጋቸውን ገልጸዋል፡፡

አረንጓዴ ቦታዎች፣ የጤናና የትምህርት ተቋማትን ጨምሮ የተለያዩ መሰረተ ልማቶችን የማሟላት ተግባራት መከናወናቸውን ነው ከንቲባ አዳነች የገለጹት።

እንደ ከንቲባ አዳነች ገለጻ በብዙሃን ትራንስፖርት አቅርቦት የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት የትራንስፖርት አቅርቦትን የማሳደግ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው።

ለአብነትም ባለፉት ስድስት ወራት 100 አዳዲስ የኤሌክትሪክ አውቶብሶች ወደ ስራ መግባታቸውን ጠቁመው በቀን 1 ሺህ 408 አውቶብሶችን በማሰማራት አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑንም አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025