
አዲስ አበባ፤ የካቲት 12/2017(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ በ2017 በጀት ዓመት ስድስት ወራት በሰው ተኮርና በጎ ፈቃድ አገልግሎት 1 ሚሊዮን 197 ሺህ 413 ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናገሩ።
የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 4ኛ የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ጉባኤ ተካሂዷል።

ከንቲባ አዳነች በመዲናዋ ባለፉት ስድስት ወራት በየዘርፉ የተያዙ እቅዶችን አፈጻጸም ለምክር ቤቱ አቅርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
በዚህም የበጎ ፍቃድና ሰው ተኮር አገልግሎት ለዘላቂ ልማት የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ ለማሳደግ በተከናወኑ ተግባራት የዜጎችን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ውጤቶች ተገኝተዋል ብለዋል።
በመዲናዋ የተለያዩ ቦታዎች በተቋቋሙ 24 የተስፋ ብርሃን የምገባ ማዕከላት በየቀኑ 36 ሺህ ለሚደርሱ ወገኖች የምገባ መርሃ ግብር እየተከናወነ መሆኑንም ጠቁመዋል።
እንዲሁም በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ ዜጎች፣ አረጋዊያን፣አቅመ ደካሞች፣ የአገር ባለውለታዎችን ጨምሮ 3 ሺህ 737 ቤቶችን በመገንባት 20 ሺህ 484 ቤተሰቦችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉንም አመልክተዋል።
ከቤት ልማት አኳያም በመንግሥት አስተባባሪነት፣ በግል አልሚዎችና በሪል ስቴት አማራጮች 27 ሺህ 304 ቤቶች መገንባታቸውንም ጠቅሰዋል።
በበጀት ዓመቱ ግማሽ ዓመት ሁለተኛው የኮሪደር ልማት ሥራ ስኬታማ በሆነ መልኩ መከናወኑን ያነሱ ሲሆን በኮሪደር ልማት ምክንያት ለሚነሱ ዜጎችና የንግድ ተቋማት ምትክ ቦታ መሰጠቱን ተናግረዋል።
ለልማት ተነሺዎች የመኖሪያ ቤቶች እንዲሁም መሥሪያ ሼዶች ተደራሽ መደረጋቸውን ገልጸዋል፡፡
አረንጓዴ ቦታዎች፣ የጤናና የትምህርት ተቋማትን ጨምሮ የተለያዩ መሰረተ ልማቶችን የማሟላት ተግባራት መከናወናቸውን ነው ከንቲባ አዳነች የገለጹት።
እንደ ከንቲባ አዳነች ገለጻ በብዙሃን ትራንስፖርት አቅርቦት የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት የትራንስፖርት አቅርቦትን የማሳደግ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው።
ለአብነትም ባለፉት ስድስት ወራት 100 አዳዲስ የኤሌክትሪክ አውቶብሶች ወደ ስራ መግባታቸውን ጠቁመው በቀን 1 ሺህ 408 አውቶብሶችን በማሰማራት አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑንም አብራርተዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026