ቦንጋ፤ የካቲት 14/2017(ኢዜአ)፡- የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በምግብ ዋስትና መርሀ ግብር የታቀፉ ወገኖችን ወደ ምርታማነት በማሸጋገር ለአደጋ የማይበገር ማህበረሰብ ለመፍጠር እየሰራ መሆኑን የክልሉ የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አስታወቀ።
የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ለማ መሠለ(ዶ/ር) እንዳሉት በክልሉ በምግብ ዋስትና ፕሮጀክት የታቀፉ ወገኖችን ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለማሸጋገር እየተሰራ ነው።
በዚህም ለአደጋ የማይበገር ማህበረሰብ ለመፍጠር የመካከለኛ ጊዜ ስትራቴጂ ዕቅድ ተቀርጾ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።
ባለፉት ሁለት ዓመታት በምግብ ዋስትና ፕሮጀክት የታቀፉ 23ሺህ 660 የሚጠጉ ወገኖች በተሰማሩበት የሥራ መስክ በቋሚነት ራሳቸውን የሚችሉበት አቅም እንዲፈጥሩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው ብለዋል።
በፕሮጀክቱ ከታቀፉት ውስጥ በዚህ ዓመት 3ሺህ 170 አባውራዎች በተሰማሩበት የሥራ መስክ ውጤታማ ሆነው እንደሚመረቁ ጠቁመው፣ ቀሪዎቹ በሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት ሙሉ በሙሉ እንደሚመረቁ አክለዋል።
በዚህም የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊ አቅም በማሳደግ እርስ በእርስ የሚደጋገፉበትና ምርታማነታቸውን በመጨመር የአደጋ ተጋላጭነትን የሚቋቋሙበት አቅም ለመፍጠር ትኩረት መሰጠቱን ጠቁመዋል።
በሌላ በኩል በክልሉ ሊከሰቱ የሚችሉ ተፈጥሯዊ አደጋዎችን ቀድሞ ለመከላከል ከሚሰራው ሥራ ጎን ለጎን ለተከሰቱ አደጋዎች በራስ አቅም ምላሽ መስጠት የሚያስችል አቅም መፈጠሩን ተናግረዋል።
ማህበረሰቡ ተፈጥሯዊ አደጋዎችን መቋቋምና በራሱ ምላሽ መስጠት የሚያስችል አቅም እየተፈጠረ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የዳውሮና ኮንታ ዞን አስተዳዳሪዎች ናቸው።
ለተግባራዊነቱም የተረጂነት አመለካከትን በማስቀረት ምርታማነትን ማሳደግ ላይ ትኩረት መሰጠቱን የዳውሮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ገበየሁ ተናግረዋል።
ከዚህ አንጻር ለሚከሰቱ የተፈጥሮ አደጋዎች የሚያስፈልግ የምግብ አቅርቦት በራስ አቅም መሸፈን የሚያስችል የመጠባበቂያ ክምችት ዞኑ በራሱ አቅም ማጎልበቱን ጠቅስዋል።
የኮንታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታከለ ተስፉ በበኩላቸው እርስ በእርስ የመረዳዳት ባህልን በማጠናከር ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ ነው ብለዋል።
ለአደጋ ጊዜ የሚሆን መጠባበቂያ ሀብት በአይነትና በገንዘብ በማሰባሰብ ለችግር ተጋላጭ ለሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች ጊዜያዊ ድጋፍ ከማድረግ ባለፈ ወደ ምርታማነት ለማሸጋጋር እየተሰራ መሆኑንም አስረድተዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025