
ቦንጋ፤ የካቲት 14/2017(ኢዜአ)፡- የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በምግብ ዋስትና መርሀ ግብር የታቀፉ ወገኖችን ወደ ምርታማነት በማሸጋገር ለአደጋ የማይበገር ማህበረሰብ ለመፍጠር እየሰራ መሆኑን የክልሉ የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አስታወቀ።
የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ለማ መሠለ(ዶ/ር) እንዳሉት በክልሉ በምግብ ዋስትና ፕሮጀክት የታቀፉ ወገኖችን ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለማሸጋገር እየተሰራ ነው።
በዚህም ለአደጋ የማይበገር ማህበረሰብ ለመፍጠር የመካከለኛ ጊዜ ስትራቴጂ ዕቅድ ተቀርጾ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።
ባለፉት ሁለት ዓመታት በምግብ ዋስትና ፕሮጀክት የታቀፉ 23ሺህ 660 የሚጠጉ ወገኖች በተሰማሩበት የሥራ መስክ በቋሚነት ራሳቸውን የሚችሉበት አቅም እንዲፈጥሩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው ብለዋል።
በፕሮጀክቱ ከታቀፉት ውስጥ በዚህ ዓመት 3ሺህ 170 አባውራዎች በተሰማሩበት የሥራ መስክ ውጤታማ ሆነው እንደሚመረቁ ጠቁመው፣ ቀሪዎቹ በሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት ሙሉ በሙሉ እንደሚመረቁ አክለዋል።
በዚህም የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊ አቅም በማሳደግ እርስ በእርስ የሚደጋገፉበትና ምርታማነታቸውን በመጨመር የአደጋ ተጋላጭነትን የሚቋቋሙበት አቅም ለመፍጠር ትኩረት መሰጠቱን ጠቁመዋል።
በሌላ በኩል በክልሉ ሊከሰቱ የሚችሉ ተፈጥሯዊ አደጋዎችን ቀድሞ ለመከላከል ከሚሰራው ሥራ ጎን ለጎን ለተከሰቱ አደጋዎች በራስ አቅም ምላሽ መስጠት የሚያስችል አቅም መፈጠሩን ተናግረዋል።
ማህበረሰቡ ተፈጥሯዊ አደጋዎችን መቋቋምና በራሱ ምላሽ መስጠት የሚያስችል አቅም እየተፈጠረ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የዳውሮና ኮንታ ዞን አስተዳዳሪዎች ናቸው።

ለተግባራዊነቱም የተረጂነት አመለካከትን በማስቀረት ምርታማነትን ማሳደግ ላይ ትኩረት መሰጠቱን የዳውሮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ገበየሁ ተናግረዋል።
ከዚህ አንጻር ለሚከሰቱ የተፈጥሮ አደጋዎች የሚያስፈልግ የምግብ አቅርቦት በራስ አቅም መሸፈን የሚያስችል የመጠባበቂያ ክምችት ዞኑ በራሱ አቅም ማጎልበቱን ጠቅስዋል።

የኮንታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታከለ ተስፉ በበኩላቸው እርስ በእርስ የመረዳዳት ባህልን በማጠናከር ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ ነው ብለዋል።
ለአደጋ ጊዜ የሚሆን መጠባበቂያ ሀብት በአይነትና በገንዘብ በማሰባሰብ ለችግር ተጋላጭ ለሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች ጊዜያዊ ድጋፍ ከማድረግ ባለፈ ወደ ምርታማነት ለማሸጋጋር እየተሰራ መሆኑንም አስረድተዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026