የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>ክልሉ በምግብ ዋስትና መርሀ ግብር የታቀፉ ወገኖችን ወደ ምርታማነት ለማሸጋገር እየሰራ ነው</p>

Feb 21, 2025

IDOPRESS

ቦንጋ፤ የካቲት 14/2017(ኢዜአ)፡- የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በምግብ ዋስትና መርሀ ግብር የታቀፉ ወገኖችን ወደ ምርታማነት በማሸጋገር ለአደጋ የማይበገር ማህበረሰብ ለመፍጠር እየሰራ መሆኑን የክልሉ የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አስታወቀ።

የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ለማ መሠለ(ዶ/ር) እንዳሉት በክልሉ በምግብ ዋስትና ፕሮጀክት የታቀፉ ወገኖችን ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለማሸጋገር እየተሰራ ነው።

በዚህም ለአደጋ የማይበገር ማህበረሰብ ለመፍጠር የመካከለኛ ጊዜ ስትራቴጂ ዕቅድ ተቀርጾ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።

ባለፉት ሁለት ዓመታት በምግብ ዋስትና ፕሮጀክት የታቀፉ 23ሺህ 660 የሚጠጉ ወገኖች በተሰማሩበት የሥራ መስክ በቋሚነት ራሳቸውን የሚችሉበት አቅም እንዲፈጥሩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው ብለዋል።

በፕሮጀክቱ ከታቀፉት ውስጥ በዚህ ዓመት 3ሺህ 170 አባውራዎች በተሰማሩበት የሥራ መስክ ውጤታማ ሆነው እንደሚመረቁ ጠቁመው፣ ቀሪዎቹ በሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት ሙሉ በሙሉ እንደሚመረቁ አክለዋል።

በዚህም የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊ አቅም በማሳደግ እርስ በእርስ የሚደጋገፉበትና ምርታማነታቸውን በመጨመር የአደጋ ተጋላጭነትን የሚቋቋሙበት አቅም ለመፍጠር ትኩረት መሰጠቱን ጠቁመዋል።

በሌላ በኩል በክልሉ ሊከሰቱ የሚችሉ ተፈጥሯዊ አደጋዎችን ቀድሞ ለመከላከል ከሚሰራው ሥራ ጎን ለጎን ለተከሰቱ አደጋዎች በራስ አቅም ምላሽ መስጠት የሚያስችል አቅም መፈጠሩን ተናግረዋል።

ማህበረሰቡ ተፈጥሯዊ አደጋዎችን መቋቋምና በራሱ ምላሽ መስጠት የሚያስችል አቅም እየተፈጠረ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የዳውሮና ኮንታ ዞን አስተዳዳሪዎች ናቸው።


ለተግባራዊነቱም የተረጂነት አመለካከትን በማስቀረት ምርታማነትን ማሳደግ ላይ ትኩረት መሰጠቱን የዳውሮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ገበየሁ ተናግረዋል።

ከዚህ አንጻር ለሚከሰቱ የተፈጥሮ አደጋዎች የሚያስፈልግ የምግብ አቅርቦት በራስ አቅም መሸፈን የሚያስችል የመጠባበቂያ ክምችት ዞኑ በራሱ አቅም ማጎልበቱን ጠቅስዋል።


የኮንታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታከለ ተስፉ በበኩላቸው እርስ በእርስ የመረዳዳት ባህልን በማጠናከር ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ ነው ብለዋል።

ለአደጋ ጊዜ የሚሆን መጠባበቂያ ሀብት በአይነትና በገንዘብ በማሰባሰብ ለችግር ተጋላጭ ለሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች ጊዜያዊ ድጋፍ ከማድረግ ባለፈ ወደ ምርታማነት ለማሸጋጋር እየተሰራ መሆኑንም አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026