
ደምቢ ዶሎ፤ የካቲት 14/2017(ኢዜአ)፦ የደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ የአካባቢው ነዋሪዎች በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ተጠቃሚ እንዲሆን እገዛ እያደረገ መሆኑን አስታወቀ፡፡
የዩኒቨርሲቲው አስተዳዳር እና ቢዝነስ ልማት ምክትል ፕሬዚዳንት ገመቺስ ብርሃኑ (ዶ/ር) ለኢዜአ አንደተናገሩት ዩኒቨርሲቲው የተማረ የሰው ሀብት ከማፍራት በተጓዳኝ የምርምርና የማህበረሰብ አገልግሎት በትኩረት እያከናወነ ይገኛል፡፡
በተለይም የአካባቢውን ነዋሪ ተጠቃሚ ለማድረግ በትምህርት፣ በግብርናና በማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ሰፋፊ ስራዎች እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በተለይም የአካባቢው ነዋሪዎች በእንሰሳት፣ በዓሳ እና በአሳማ እርባታ ተጠቃሚ እንዲሆኑ በምርምር የተገኙ የተሻሻሉ ዝርያዎች እያቀረበ መሆኑን ገልጸዋል።
በቡና፣ በአትክልት እና ፍራፍሬ እና በሌሎችም የግብርና ዘርፎች በዩኒቨርሲቲው የምርምር ማዕከሎች የተገኙ የተሻሻሉ ዝርያዎች እየቀረቡ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ዩኒቨርሲቲው በ10 ሄክታር መሬት ላይ የተለያዩ የግብርና ስራዎች እያከናወነ መሆኑን አንስተው የአካባቢውን ማህበረሰብ ከማገዝ ባሻገር ዩኒቨርሲቲው በራሱ አቅም ገቢ ለማመንጫት ጥረት እያደረገ መሆኑንም አክለዋል።

በተጨማሪም በቄለም ወለጋ ዞን በኢኒሼቲቭ መልክ የሚተገበረውን የንብ ማነብ ስራ ለማገዝ የተለያዩ ድጋፎች እተቀረበ መሆኑን ጨምረው ገልጸዋል።
የደምቦ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ ግብርና ምርምር ማዕከል ዳይሬክተር ሶሬሳ ሹማ፣ ዩኒቨርስቲው የሚደግፈው የአሳ እርባታ ስራ የአካባቢው ነዋሪ ተጨማሪ ገቢ እንዲያገኝ እያስቻለ ነው ብለዋል።

ከእንስሳት እርባታ ባሻገር ነዋሪው የአሳ እርባታ ስራን እንዲለማመድ በተደረገው እገዛ ማህበረሰቡ የተመጣጠነ የምግብ እንዲያገኝ እድል መፈጠሩንም ተናግረዋል።
ዩኒቨርስቲው የሚያከናውናቸው የግብርና ምርምር ስራዎች በአካባቢው የሌማት ትሩፋትን ከማገዝ ጎን ለጎን ለወጣቶች የስራ እድል መፈጠሩንም ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026