የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>ዩኒቨርሲቲው የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ተሳታፊዎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ እያገዘ ነው</p>

Feb 21, 2025

IDOPRESS

ደምቢ ዶሎ፤ የካቲት 14/2017(ኢዜአ)፦ የደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ የአካባቢው ነዋሪዎች በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ተጠቃሚ እንዲሆን እገዛ እያደረገ መሆኑን አስታወቀ፡፡


የዩኒቨርሲቲው አስተዳዳር እና ቢዝነስ ልማት ምክትል ፕሬዚዳንት ገመቺስ ብርሃኑ (ዶ/ር) ለኢዜአ አንደተናገሩት ዩኒቨርሲቲው የተማረ የሰው ሀብት ከማፍራት በተጓዳኝ የምርምርና የማህበረሰብ አገልግሎት በትኩረት እያከናወነ ይገኛል፡፡


በተለይም የአካባቢውን ነዋሪ ተጠቃሚ ለማድረግ በትምህርት፣ በግብርናና በማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ሰፋፊ ስራዎች እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡


በተለይም የአካባቢው ነዋሪዎች በእንሰሳት፣ በዓሳ እና በአሳማ እርባታ ተጠቃሚ እንዲሆኑ በምርምር የተገኙ የተሻሻሉ ዝርያዎች እያቀረበ መሆኑን ገልጸዋል።


በቡና፣ በአትክልት እና ፍራፍሬ እና በሌሎችም የግብርና ዘርፎች በዩኒቨርሲቲው የምርምር ማዕከሎች የተገኙ የተሻሻሉ ዝርያዎች እየቀረቡ መሆኑን ጠቅሰዋል።


ዩኒቨርሲቲው በ10 ሄክታር መሬት ላይ የተለያዩ የግብርና ስራዎች እያከናወነ መሆኑን አንስተው የአካባቢውን ማህበረሰብ ከማገዝ ባሻገር ዩኒቨርሲቲው በራሱ አቅም ገቢ ለማመንጫት ጥረት እያደረገ መሆኑንም አክለዋል።


በተጨማሪም በቄለም ወለጋ ዞን በኢኒሼቲቭ መልክ የሚተገበረውን የንብ ማነብ ስራ ለማገዝ የተለያዩ ድጋፎች እተቀረበ መሆኑን ጨምረው ገልጸዋል።


የደምቦ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ ግብርና ምርምር ማዕከል ዳይሬክተር ሶሬሳ ሹማ፣ ዩኒቨርስቲው የሚደግፈው የአሳ እርባታ ስራ የአካባቢው ነዋሪ ተጨማሪ ገቢ እንዲያገኝ እያስቻለ ነው ብለዋል።


ከእንስሳት እርባታ ባሻገር ነዋሪው የአሳ እርባታ ስራን እንዲለማመድ በተደረገው እገዛ ማህበረሰቡ የተመጣጠነ የምግብ እንዲያገኝ እድል መፈጠሩንም ተናግረዋል።


ዩኒቨርስቲው የሚያከናውናቸው የግብርና ምርምር ስራዎች በአካባቢው የሌማት ትሩፋትን ከማገዝ ጎን ለጎን ለወጣቶች የስራ እድል መፈጠሩንም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026